Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ወደ ፓሪስ ለሚያቀናው የኢትዮጵያ ልዑክ በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ከነገ በስቲያ ሽኝት ይደረጋል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ ለሚሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን የፊታችን ሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት የክብር ሽኝት እንደሚደረግ ተመላከተ፡፡ በሽኝት ሥነ-ሥርዓቱ ላይም ፕሬዚዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እንደሚገኙ መገለጹን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡ በዚሁ ወቅትም የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክቶችና የሰንደቅ ዓላማ ርክክብ እንደሚኖር ተጠቁሟል፡፡
Read More...

በሚቀጥለው ወር ዓለም አቀፍ የቦክስ ሻምፒዮና በኢትዮጵያ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ዓለም አቀፍ የቦክስ ሻምፒዮና በሚቀጥለው ወር በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የአፍሪካ ቦክስ ኮንፌደሬሽን አስታወቀ። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ እና የአፍሪካ ቦክስ ኮንፌደሬሽን ዳይሬክተር አሊሳ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ÷ ዓለም አቀፍ የቦክስ ሻምፒዮናን በኢትዮጵያ ለማካሄድ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።…

የባርሴሎና ደጋፊዎች ኒኮ ዊሊያምስን ለማስፈረም በቲክቶክ ገንዘብ ማዋጣት ጀመሩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የባርሴሎና ደጋፊዎች ኒኮ ዊሊያምስን ለማስፈረም በክለቡ ይፋዊ የቲክቶክ አካውንት ገንዘብ ማሰባሰብ መጀመራቸው ተገለፀ፡፡ የአትሌቲክ ቢልባኦ እግር ኳስ ክለብ ንብረት የሆነው የ22 ዓመቱ ኒኮ ዊሊያምስ የአውሮፓ ዋንጫ አሸናፊ በሆነው የስፔን ብሄራዊ ቡድን ስኬታማ ጊዜን ማሳለፉ የሚታወስ ነው፡፡ በዚህም ወጣቱ የመስመር አጥዊ…

ሉካ ሞድሪች ለተጨማሪ አንድ ዓመት ውሉን አራዘመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሪያል ማድሪዱ አማካይ ሉካ ሞድሪች በሳንትያጎ ቤርናቢዩ ለተጨማሪ አንድ ዓመት የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡ በፈረንጆቹ 2012 ከእንግሊዙ ቶተንሃም ሆትስፐርስ ሪያል ማድሪድን የተቀላቀለው የ38 ዓመቱ ክሮሺያዊው አማካይ ሉካ ሞድሪች፤ ለ12 የውድድር ዓመታት የሎስ ብላንኮዎቹ የቡድን ድምቀት መሆን ችሏል፡፡ በቆይታው…

አርጀንቲናውያን ተጫዋቾች በፈረንሳይ ተጫዋቾች ላይ የሰነዘሩት የዘረኝት ጥቃት ከፍተኛ ቁጣ አስነሳ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች የዘር ሐረጋቸው ከአፍሪካ የሚመዘዝ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ላይ ያነጣጠረ የዘረኝነት ዘፈን ሲዘፍኑ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል በማህበራዊ ትስስር ገፆች ከተሰራጨ በኋላ ከፍተኛ ቁጣ አስነስቷል፡፡ የፈረንሳይ እግር ኳስ ፌዴሬሽንም የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን አባላት ‹‹አስፀያፊ፣…

የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚጀምርበት ቀን ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር መስከረም 10 ቀን 2017 እንደሚጀምር ተገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማኅበር ፕሪሚየር ሊጉ የሚጀመርበትን ጊዜ ለተሳታፊ ክለቦች ማሳወቁን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል፡፡ የ2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ሰኔ 29 ቀን 2016 መጠናቀቁ…

ሳውዝጌት ከእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝነታቸው ለቀቁ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት በራሳቸው ፈቃድ ኃላፊነታቸውን ለቀቁ፡፡ ሳውዝ ጌት ከፈረንጆቹ 2016 ጀምሮ የእግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው አገልግለዋል፡፡ ከስምንት ዓመታት በኋላም በይፋ ከብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝነታቸው መልቀቃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ በቡድኑ በነበራቸው ቆይታም በ2024ቱ…