ስፓርት
አትሌት ለተሰንበት የሴቶች 5ሺህ ሜትር ሩጫ 4ኛውን ፈጣን ሰዓት አስመዘገበች
አዲሰ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ለተሰንበት ግደይ የሴቶች 5ሺህ ሜትር ሩጫ 4ኛውን ፈጣን ሰዓት አስመዝግባለች፡፡
አትሌት ለተሰንበት ግደይ በበርሊን ኮንቲነንታል ቱር የሴቶች 5ሺህ ሜትር ሩጫ ፈጣን ሰዓት ሪከርድን ለመስበር ባትችልም 14 ደቂቃ ከ08 ሰከንድ በመግባት ነው 4ኛውን ፈጣን ሰዓቷን ያስመዘገበችው።
በሴቶች 5 ሺህ ሜትር ሩጫ አምስት ፈጣን ሰዓቶች የተመዘገቡ ሲሆን ፥ 3ቱ በአትሌት ለተሰንበት ግደይ የተመዘገቡ ናቸው።
የሴቶች 5ሺህ ሜትር ሩጫ ሪከርድ ፈጣን ሰዓት 14፡05 ሲሆን ፥ በኬኒያዊቷ አትሌት…
Read More...
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሳምንቱ ታላቅ ጨዋታ ዛሬ ምሽት ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ከማንቼስተር ዩናይትድ የሚያደርጉት ጨዋታ ምሽት 12፡30 ላይ ይካሄዳል፡፡
በአርሰናል በኩል ቶማስ ፓርቴይ፣ ጁሪየን ቲምበር እና ሞሃመድ ኤልነኒ በጉዳት ምክንያት የማይሰለፉ ሲሆን÷ በአንፃሩ በጉዳት የቆየው ጋብሬል ማጋሌሽ የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደርግል፡፡
አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ በጉዳት…
ማንቼስተር ዩናይትድ ሶፊያን አሙራባትን ከፊዮረንቲና በውሰት ለማስፈረም ስምምነት ላይ ደረሰ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ሞሮኳዊውን የመሀል ክፍል ተጫዋች ሶፊያን አሙራባት ከፊዮረንቲና በውሰት ለማስፈረም ስምምነት ላይ ደርሷል፡፡
በስምምነቱ መሰረት ማንቼስተር ዩናይትድ ለጣሊያኑ ክለብ 8 ነጥብ 5 ሚሊዮን ፓውንድ የውስት ውል ይከፍላል ነው የተባለው፡፡
ሶፊያን በኳታሩ የዓለም ዋንጫ ታሪካዊ ጉዞ ባደረገው የሞሮኮ ብሄራዊ…
አትሌት ለተሠንበት ግደይ በኒውዮርክ ማራቶን እንደምትካፈል ተነገረ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በፈረንጆቹ ሕዳር 5 ቀን 2023 በሚካሄደው የኒውዮርክ ማራቶን ውድድር የሴቶች የ10 ሺህ ሜትር እና የግማሽ ማራቶን የዓለም ሪከርድ ባለቤቷ አትሌት ለተሠንበት ግደይ እንደምትካፈል ተገለጸ።
አትሌት ለተሠንበት ባለፈው ዓመት በቫሌንሲያ በተካሄደው የማራቶን ሩጫ ላይ 2 ሠዓት ከ16 ደቂቃ ከ49 ሠከንድ በመግባት በታሪክ ፈጣኑን…
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የምድብ ድልድል ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2023/24 የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ምድብ ድልድል ዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት ዛሬ በፈረንሳይ ሞናኮ ተካሂዷል።
በዚህ መሰረትም፡-
በምድብ 1: ማንቸስተር ዩናይትድ ፣ ባይየርን ሙኒክ፣ ኮፐን ሃገን፣ ጋላታሳራይ
በምድብ 2፡ አርሰናል ፣ ሴቪያ፣ ፒ ኤስ ቪ፣ ሌንስ
በምድብ 3፡ ናፖሊ ፣ ሪያል ማድሪድ፣ ብራጋ፣…
በ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለተሳተፉ የአትሌቲክስ ቡድን አባላት የማበረታቻ ሽልማት እየተሰጠ ነው
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለተሳተፉ የአትሌቲክስ ቡድን አባላት የማበረታቻ ሽልማት እየሰጠ ነው።
በመርሐ ግብሩ ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ቀጄላ መርዳሳን ጨምሮ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፣ የአትሌቲክስ ልዑካን ቡድን…
ንግድ ባንክ በምስራቅ አፍሪካ የቻምፒየንስ ሊግ ማጣሪያ 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን በምስራቅ አፍሪካ የቻምፒየንስ ሊግ ማጣሪያ 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቋል፡፡
በውድድሩ ፍፃሜ የታንዛኒያውን ጀኬቲ ኩዊንስ የገጠመው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ÷ መደበኛ ጨዋታውን በአቻ ውጤት ማጠናቀቁን ተከትሎ ወደ መለያ ምት አምርተዋል፡፡
በዚህም 5 ለ 4 ተሸንፎ ዋንጫውን…