ስፓርት
ስፔን ኮስታሪካን ከግማሽ ደርዘን ጎል በላይ በማስቆጠር አሸነፈች
አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ዋንጫው አራተኛ ቀን ውሎ ስፔን ከግማሽ ደርዘን ጎል በላይ በማስቆጠር አሸንፋለች።
በምድብ 5 የተደለደለችው ስፔን የደቡብ አሜሪካዋን ኮስታሪካን 7 ለ 0 በሆነ ሰፊ የጎል ልዩነት ማሸነፍ ችላለች።
ዳኒ ኦልሞ፣ ማርኮ አሴንሲዮ፣ ጋቪ፣ ካርሎስ ሶለር እና አልቫሮ ሞራታ አንድ አንድ ጎሎችን ሲያስቆጥሩ ፌራን ቶሬስ ሁለት ጎሎችን በስሙ አስመዝግቧል።
በምድቡ ቀደም ብሎ በተካሄደ ጨዋታ የአራት ጊዜ የዓለም ዋንጫ አሸናፊዋ ጀርመን ባልተጠበቀ ሁኔታ 2 ለ 1 መሸነፏ ይታወሳል።…
Read More...
በዓለም ዋንጫ ጨዋታ ጃፓን ጀርመንን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸነፈች
አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ22ኛው ዓለም ዋንጫ የአራተኛ ቀን ውሎ በምድብ አምስት በተደረገ ጨዋታ ጃፓን ጀርመንን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡
የማንችስተር ሲቲው የአማካይ ክፍል ተጫዋች ኢልካይ ጉንዶጋን በ33ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠረው ግብ የጀርመን ብሔራዊ ቡድንን መሪ ማድረግ ችሎ ነበር።
ይሁንና ተቀይሮ የገባው የጀርመኑ…
በአራተኛ ቀን የ22ኛው የዓለም ዋንጫ ውሎ አራት ጨዋታዎች ይከናወናሉ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 14፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው የዓለም ዋንጫ የጨዋታ መርሐ ግብር አራት ጨዋታዎች ይከናወናሉ።
በዚሁ መሰረት 7 ሰዓት ላይ በምድብ ሥድስት የተደለደሉት ሞሮኮ እና ክሮሺያ ይጫወታሉ።
በተመሳሳይ በዚሁ ምድብ የሚገኙት ቤልጂየም ከካናዳ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ።
በሌላ የጨዋታ መርሐ ግብር በምድብ አምስት የተደለደሉት ጀርመን…
ሜክሲኮ እና ፖላንድ በአቻ ውጤት ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ22ኛው የዓለም ዋንጫ ምሽት ላይ በተካሄደ ጨዋታ የተገናኙት ሜክሲኮ እና ፖላንድ ያለምንም ጎል በአቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
ፖላንድ ያገኘችውን የፍጹም ቅጣት ምት ወደ ውጤት መቀየር ሳትችል ቀርታለች፡፡
የ2022 የዓለም ዋንጫ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት 4 ሰዓት ላይ ፈረንሳይ ከአውስትራሊያ ይጫወታሉ፡፡
ቀደም ሲል…
ክርስቲያኖ ሮናልዶ በስምምነት ከማንቼስተር ዩናይትድ ተለያየ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከክለቡ ጋር በደረሱት ስምምነት መሰረት ከማንቼስተር ዩናይትድ መልቀቁ ይፋ ሆኗል፡፡
ሮናልዶ በኦልትራፎርድ ቆይታው በ346 ጨዋታዎች 145 ጎሎችን በማስቆጠር ላበረከተው አስተዋፅዖ ያመሰገነው ክለቡ÷ በቀጣይ የእግር ኳስ ሕይወቱ የተሳካ እንዲሆን መልካም ምኞቱን ገልጿል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ…
ዴንማርክ እና ቱኒዚያ ያለምንም ጎል በአቻ ውጤት ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በምድብ አራት የተደለደሉት ዴንማርክ እና ቱኒዚያ ያረጉት ጨዋታ ያለምንም ጎል ተጠናቋል፡፡
10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደረጉት ዴንማርክ እና ቱኒዚያ አቻ በሆነ ውጤት መለያየታቸውን ተከትሎ ነጥብ ተጋርተዋል፡፡
በዚህም የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ከተጀመረ ጀምሮ ያለምንም ጎል የተጠናቀቀ የመጀመሪያው ጨዋታ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡…
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ድል ቀናቸው
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ሲዳማ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡
ሲዳማ ቡና መቻልን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ÷ ጎሎቹን ፍሬው ሰለሞን በ17ኛው እና ሙሉዓለም መስፍን በ75ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል፡፡
በተመሳሳይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሐዋሳ ከተማን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ጎሎቹንም÷…