ስፓርት
አርሰናል ዌስትሃም ዩናይትድን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርሰናል ዌስትሃም ዩናይትድን 1 ለ 0 በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ከ30 በተደረገ ጨዋታ የአርሰናል ግብ ሊያንድሮ ትሮሳርድ አስቆጥሯል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም አርሰናል ነጥቡን ወደ 79 ከፍ በማድረግ ከተከታዩ ማንቼስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት አስፍቷል፡፡
Read More...
ለሀላባ ከተማ ተጫዋቾች ሽልማት ተበረከተ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሀላባ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ አሸናፊ ለሆነው የሀላባ ከተማ ተጫዋቾች የገንዘብ እና የቤት መስሪያ ቦታ ሽልማት አበርክቷል፡፡
የ2018 የኢትዮጵያ ከፍተኛ አጠቃላይ የዋንጫ አሸናፊ የሆነው ሀላባ ከተማ ክለብ ወደ ሀላባ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።
ክለቡ ወደ 2019 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር…
የአየር ንብረት ለውጥ ለ2026ቱ የዓለም ዋንጫ…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ ሊካሄድ ጥቂት ጊዜያት ለቀረው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድር ፈተና ሊሆን እንደሚችል ተጠቆመ።
ውድድሩን በሚያስተናግዱ አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ያለው የአየር ንብረት በከፍተኛ ሙቀት፣ በነጎድጓዳማ ዝናብ እና በሰደድ እሳት የሚታወቅ መሆኑ ከውድድሩ መጀመር አስቀድሞ በርካቶችን እያሳሰበ ይገኛል።…
ዌስትሃም ዩናይትድ ከአርሰናል…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር የሊጉ መሪ አርሰናል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 12 ሰዓት ከ30 ላይ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል።
አርሰናል 76 ነጥቦችን በመሰብሰብ ሊጉን እየመራ ሲሆን፥ ተጋጣሚው ዌስትሃም ዩናይትድ በበኩሉ 36 ነጥቦችን በመሰብሰብ 18ኛ ደረጃን በመያዝ ወራጅ ቀጣና ላይ…
ኤልክላሲኮ – ባርሴሎና የቡድን አንድነቱን ካጣው ሪያል ማድሪድ…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የስፔን ላሊጋ መርሐ ግብር ባርሴሎናን ከሪያል ማድሪድ የሚያገናኘው ኤልክላሲኮ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት በካምፕ ኑ ይደረጋል፡፡
በቀደሙት ዓመታት ኤልክላሲኮ በከፍተኛ ጉጉት የሚጠበቅና ከፍተኛ ፉክክር የሚታይበት መርሐ ግብር ነበር፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሁለቱ ቡድኖች የእርስ በርስ ግንኙነት በቀደሙት ዓመታት…
ሃላባ ከተማ የከፍተኛ ሊጉ አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሃላባ ከተማ በመለያ ምት ጋሞ ጨንቻን 4 ለ 3 በማሸነፍ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ ሆኗል።
የ2018 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የማጠቃለያ የፍፃሜ ጨዋታ ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ተካሂዷል።
በፍፃሜው ሃላባ ከተማን ከጋሞ ጨንቻ ያገናኘው ጨዋታ በመደበኛ ክፍለ ጊዜ ያለ ግብ አቻ ተጠናቅቋል።
የዋንጫውን…
በሪያል ማድሪድ ደጋፊዎች እንዲለቅ የተፈለገው ምባፔ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጫዋች ኪሊያን ምባፔ ሪያል ማድሪድን እንዲለቅ በርካታ የክለቡ ደጋፊዎች ፊርማ እያሰባሰቡ ይገኛሉ፡፡
ምባፔ የሀገሩን ክለብ ፒኤስጂን በመልቀቅ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ፍለጋ ሪያል ማድሪድን ቢቀላቀለም በክለቡ በቆየባቸው ሁለት ዓመታት ይህንን ሕልሙን ማሳካት አልቻለም፡፡
በተቃራኒው…