ስፓርት
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2026/27 የውድድር ዘመን የጨዋታ መርሐ ግብር ይፋ ተደርጓል፡፡
ሻምፒዮኑ አርሰናል በሜዳው ኢምሬትስ ከአዲስ አዳጊው ኮቬንትሪ ሲቲ ጋር የሊጉን የመክፈቻ ጨዋታውን ያደርጋል።
በአዲሱ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ የሚመራው ማንችስተር ሲቲ በሜዳው ከ በርንማውዝ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን የሚያደርግ ይሆናል፡፡
በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ የሚመራው ማንቼስተር ዩናይትድ በበኩሉ ወደ ሊጉ ካደገው ሃል ሲቲ ጋር በመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታው ይገናኛል፡፡
አንዶኒ ኢራኦላን…
Read More...
ደቡብ አፍሪካና ቼክ ሪፐብሊክ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ አንድ 2ኛ ጨዋታ ደቡብ አፍሪካ እና ቼክ ሪፐብሊክ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
የቼክ ሪፐብሊክን ግብ ሚሼል ሳዲሌክ ሲያስቆጥር÷የደቡብ አፍሪካን የአቻነት ግብ ደግሞ ሞክዌና ከመረብ አሳርፏል፡፡
የቼክ ሪፐብሊክ ግብ በ2026 ዓለም ዋንጫ እስካሁን ከተመዘገቡት ግቦች ውስጥ…
በዓለም ዋንጫ የጋሪ ሊንከርን ክብረ ወሰን የተጋራው ሃሪ ኬን…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጫዋች ሃሪ ኬን በዓለም ዋንጫ ውድድር በርካታ ግቦችን በማስቆጠር የሀገሩን ልጅ ጋሪ ሊንከር ክብረ ወሰን ተጋርቷል፡፡
በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ትናንት ምሽት እንግሊዝ ክሮሺን 4 ለ 2 ማሸነፏ ይታወቃል፡፡…
ሪያል ማድሪድ በርናርዶ ሲልቫን አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ ፖርቹጋላዊውን አማካይ በርናርዶ ሲልቫ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡
ባለፉት ዓመታት በማንቼስተር ሲቲ ስኬታማ ጊዜን ያሳለፈው ሲልቫ በነጻ ዝውውር ነው ሪያል ማድሪድን የተቀላቀለው፡፡
ተጫዋቹ እስከ ፈረንጆቹ 2028 የሚያቆየውን የሁለት ዓመት ኮንትራት ውል መፈረሙን ክለቡ…
በዓለም ዋንጫ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰንን የተጋራው ሊዮ ሜሲ..
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በስድስት የዓለም ዋንጫ ውድድሮች በመጫወት ክብረወሰን ያስመዘገበው ሊዮኔል ሜሲ በ16 ግቦች የዓለም ዋንጫ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን ክብረ ወሰን ተጋርቷል፡፡
በፈረንጆቹ 2006 በጀርመን ዓለም ዋንጫ በ18 አመቱ ሀገሩን ወክሎ መጫወት የጀመረው የሮዛሪዮው ተወላጅ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ የዘንድሮውን ጨምሮ በስድስት…
ፖርቹጋል ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ..
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የክሪስቲያኖ ሮናልዶ ሀገር ፖርቹጋል የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋን ዛሬ ምሽት ታደርጋለች፡፡
ፖርቹጋል ምሽት 2 ሰዓት ላይ ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ጋር በሂውስተን ስታዲየም በምታደርገው ጨዋታ የማሸነፍ ቅድመ ግምት ተሰጥቷታል፡፡
የመጨረሻው የዓለም ዋንጫ ተሳትፎውን የሚያደርገው ፖርቹጋላዊ…
ሜሲ እና ምባፔ የምንጊዜም የዓለም ዋንጫ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ለመሆን…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በፈረንጆቹ 1930 መደረግ በጀመረው የዓለም ዋንጫ ውድድር ጀርመናዊው ሚሮስላቭ ክሎስ የመድረኩን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃን እየመራው ይገኛል፡፡
የጀርመን ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ ኮከብ ሚሮስላቭ ክሎስ በዓለም ዋንጫ ውድድር 24 ጨዋታዎችን አድርጎ 16 ግቦችን በማስቆጠር የዓለም ዋንጫ የምን ጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች…