Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በፕሪሚየርሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲዳማ ቡናን 5 ለ 1 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲዳማ ቡናን 5 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል፡፡ በባህርዳር ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኢስማኤል ኦሮ አጉሮ ሀትሪክ ሲሰራ÷ በረከት ወልዴ እና አማኑኤል ገብረሚካኤል የጊዮርጊስን የማሸነፊያ ግቦች አስቆጥረዋል፡፡ ፈረሰኞች ሲዳማ ቡናን ማሸነፋቸውን ተከትሎ በ9 ነጥብ መሪነታቸውን አጠናክረዋል፡፡ በተመሳሳይ ወላይታ ዲቻ እና ኢትዮኤሌክትሪክ  በዛሬው ዕለት ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ  በሆነ ውጤት ተጠናቋል፡፡
Read More...

ኬንያዊው አትሌት ፊሌሞን ካቼራን አበረታች ንጥረ-ነገር በመጠቀሙ ለሦስት ዓመታት ከውድድር ታገደ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ኬንያዊው አትሌት ፊሌሞን ካቼራን አበረታች ንጥረ-ነገር ተጠቅሞ በመገኘቱ ለሦስት ዓመታት ከውድድር ታገደ፡፡ የአበረታች ንጥረ-ነገር ምርመራ ሳይደረግለት እና በ”አትሌቲክስ ኢንተግሪቲ ዩኒት” ሳይታገድ በፊት አትሌቱ በጋራ ብልፅግና ሀገራት (ኮመንዌልዝ) ውድድሮች ላይ ለመሳተፍ የኬንያን የማራቶን ቡድን አባላት ተቀላቅሎ…

የብራይተኑ አማካይ ኢኖክ ምዌፑ በልብ ሕመም ምክንያት በ24 ዓመቱ ጫማ ሊሰቅል ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛምቢያዊው የብራይተን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ኢኖክ ምዌፑ ባጋጠመው የልብ ሕመም በ24 ዓመቱ ከእግር ኳስ ዓለም ሊገለል መሆኑ ተሰማ፡፡ ምዌፑ ከቤተሰብ በዘር ሊተላለፍ በሚችል የልብ ሕመም ምክንያት ከእግር ኳስ ዓለም እንደሚርቅ ክለቡ አስታውቋል። እግር ኳስ መጫወቱን የማያቆም ከሆነ ለሕይወቱ አስጊ መሆኑንም ነው…

በሴካፋ ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ውድድር ደቡብ ሱዳን ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበራት (ሴካፋ) ደቡብ ሱዳን ወደ ግማሽ ፍጻሜ ማለፏን አረጋግጣለች። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም እየተከናወነ የሚገኘውና ሰባተኛ ቀኑን በያዘው ውድድር ÷ ዛሬ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ተካሄደዋል። በምድብ ሁለት ደቡብ ሱዳንና…

የፋሲል ከነማና ሴፋክሲያን ጨዋታ 0 ለ 0 ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፋሲል ከነማና ሴፋክሲያን በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ያደረጉት የማጣሪያ ጨዋታ 0 ለ 0 ተጠናቋል፡፡ አጼዎቹ በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የሁለተኛ ዙር ማጣሪያ ከቱኒዚያው ሴፋክሲያን ጋር ዛሬ አድርገዋል። ጨዋታውን በባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም አፄዎቹ የሜዳቸውን እድል መጠቀም አልቻሉም። ፋሲል ከነማና…

ዛሬ ሁለት የሴካፋ ውድድር ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሴካፋ ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ውድድር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበራት ምክር ቤት (ሴካፋ) ከመስከረም 23 ቀን 2015 ጀምሮ በአበበ በቂላ ስታዲየም እየተካሄደ ይገኛል። በዚህም ዛሬ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች የሚከናወኑ…

በፕሪሚየር ሊጉ ሀዲያ ሆሳዕና እና አዳማ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሁለተኛው ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀዲያ ሆሳዕና እና አዳማ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል፡፡ ዛሬ ምሳ ሰዓትና ከከሰዓት በኋላ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡ በዚህም 7 ሰዓት ሀዲያ ሆሳዕና ከሲዳማ ቡና ጨዋታቸውን ያደረጉ ሲሆን÷ ሀዲያ ሆሳዕና 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የሀዲያ ሆሳዕናን…