Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ የ10ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በቀጣይ ሳምንት ይጀምራሉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ የ10ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ በድሬዳዋ ከተማ መካሄድ ይጀምራሉ፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ የዘጠኝ ሳምንታት ጨዋታዎች በሀዋሳ ከተማ የተካሄዱ ሲሆን ፥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ ዝግጅትን ተከትሎ ታህሣሥ 15 መቋረጡ ይታወሳል። የሊጉ አስተዳዳሪ አካልም በጊዜያዊነት አፍሪካ ዋንጫው ከተጠናቀቀ ከአምስት ቀናት በኋላ ሊጉን ለመቀጠል አቅዶ የነበረ ቢሆንም ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ መሰናበቱን ተከትሎ የሊጉን የመጀመሪያ…
Read More...

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ዛንዚባር ገባ

አዲስ አበባ፣ጥር 13፣2014 (ኤፍ ቢሲ)የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ዛንዚባር መግባቱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡ ከታንዛኒያ አቻው ጋር ለሚያደርገው የ2022 ዓለም ዋንጫ የ4ኛው ዙር የማጣሪያ ጨዋታ ዛሬ ከረፋዱ 4 ሰዓት ከአዲስ አበባ በመነሳት ወደ ታንዛኒያ ጉዞውን አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ከ20…

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ በአፍሪካ ዊልቼር ቅርጫት ኳስ ውድድር ላይ የሚሳተፈውን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አበረታቱ

አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የአፍሪካ ዊልቼር ቅርጫት ኳስ ውድድር ላይ የሚሳተፈውን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አባላትን በአካል በመገኘት አበረታቱ። ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በምታስተናግደው 11ኛው የአፍሪካ ዊልቼር ቅርጫት ኳስ ውድድር ላይ ብሔራዊ ቡድኗ በሁለቱም ፆታ ለማሳተፍ በዝግጅት ላይ ትገኛለች።…

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ተሰናበተ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ተሰናበተ፡፡ ዋልያዎቹ ዛሬ ከቡርኪናፋሶ አቻቸው ጋር አንድ እኩል ቢለያዩም በአንድ ነጥብ የምድቡን የመጨረሻ ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል፡፡ ለኢትዮጵያ በፍጹም ቅጣት ምት ብቸኛዋን ጎል በ52ኛው ደቂቃ ላይ ጌታነህ ከበደ አስቆጥሯል፡፡ ኢትዮጵያን፦ እናልማ፤…

ዋልያዎቹ ከቡርኪናፋሶ ጋር እያደረጉት ባለው ጨዋታ 1 ለ 0 እየተመሩ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከቡርኪናፋሶ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ እየተካሄደ ነው፡፡ በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ የተጠናቀቀ ሲሆን፥ ዋልያዎቹ 1 ለ 0 እየተመሩ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የመጀመሪያ ሁለት የምድቡ ጨዋታዎችን መሸነፉ የሚታወስ ሲሆን፥ በአፍሪካ ዋንጫው ያለፉትን 11 ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም ፡፡…

ፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ያዘጋጀው የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ በጎንደር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ያዘጋጀው የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ በጎንደር ከተማ ተካሄደ። ለስፖርት ክለቡ ሃብት ማሰባሰቢያ በየዓመቱ የሚያዘጋጀው የጎዳና ላይ ሩጫው የዘንድሮው መርሃ ግብር መነሻውን ማራኪ ፕላዛ ሆቴል አድርጎ መስቀል አደባባይ መጠናቀቂያውን አድርጓል፡፡ በጎዳና ላይ ሩጫው ከ10 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች…

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ባፉሳም ከተማ ገባ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በካሜሮኗ ባፉሳም ከተማ መግባቱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስታወቀ። ዋልያዎቹ ያለፉትን ሀያ ቀናት የቆዩበት ያውንዴ ከተማን በመልቀቅ የምድቡን ሶስተኛ ጨዋታ የሚያከናውኑበት ባፉሳም ከተማ ዛሬ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር 9:10 ላይ ደርሰዋል። የቡድኑ አባላት በስፍራው ሲደርሱ…