Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የሴኔጋሉ ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል የዛሬው ሰኞ የሀገሪቱ የድል በዓል አንዲሆን ወሰኑ

አዲስ አበባ፣ ጥር 30፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሴኔጋል ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል የሀገሪቱ ብሄራዊ ቡድን በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ መሆኑን ተከትሎ ድሉን ለማክበር የዛሬው ሰኞ ብሄራዊ በዓል አንዲሆን ወስነዋል።   ሀገራቸው ሴኔጋል ግብፅን በመለያ ምት 4 ለ 2 በማሸነፍ ዋንጫውን ስታነሳ በ 35ኛዉ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ለመሳተፍ አዲስ አበባ የነበሩት ማኪ ሳል የዛሬውን ሰኞ የሀገሪቱ የድል በዓል አንዲሆን መወሰናቸውን በሀገሪቱ ቴሌቪዥን አስታውቀዋል፡፡   አዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ማኪ…
Read More...

ሻምፒዮን መሆን ልዩ ትርጉም አለው፣በአፍሪካ ስኬታማ ቡድንን ማሸነፍ ደግሞ ሌላ ስሜት ይሰጣል -አሊዮ ሲሴ

አዲስ አበባ፣ጥር 29፣2014 (ኤፍ ቢሲ) የሴኔጋል ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ አሊዩ ሲሴ በተጫዋችነት ዘመኑ የናፈቀዉን አፍሪካ ዋንጫ በአሰልጣኝነት አጣጥሞታል፡፡ የቀድሞው የሴኔጋል ብሄራዊ ቡድን ተጫዋች አሊዮ ሲሴ በተጨዋችነት ዘመኑ በ23ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከካሜሮን ጋር በነበረ የፍፃሜ ጨዋታ መለያ ምት መሳቱን ተከትሎ ቡድኑ ዋንጫዉን አጥቷል፡፡ ሲሴ ከፀፀት…

በ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ  ሴኔጋል ሻምፒዮን ሆናለች

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ ) በ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ  ሴኔጋል ሻምፒዮን ሆናለች። ሴኔጋል ግብፅን በመለያ ምት 4 ለ 2 በማሸነፍ ዋንጫውን ለመጀመሪያ ጊዜ አንስታለች። ጎል ያልተቆጠረበት የ120 ትንቅንቅ ወደ መለያ ምት አምርቶ የቲሪንጋ አንበሶቹ ሴኔጋል ድል ቀንቷቸዋል፡፡ በጨዋታው ብልጫ የነበራት ሴኔጋል የመጀመሪያ ዋንጫዋን በማንሳት የትሪንጋ…

የአፍሪካ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታን ደቡብ አፍሪካዊው ቪክቶር ጎሜዝ በዋና ዳኝነት ይመሩታል

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ አፍሪካዊው ኢንተርናሽናል አልቢትር ቪክቶር ጎሜዝ ዛሬ ሴኔጋልና ግብፅ የሚያደርጉትን የአፍሪካ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ እንዲዳኙ በካፍ መመረጣቸው ተገልጿል። ደቡብ አፍሪካዊው ኢንተርናሽናል ዳኛ ቪክቶር ጎሜዝ ከፈረንጆቹ 2008 ጀምሮ በደቡብ አፍሪካ ሊግ የሚደረጉ ታላላቅ ጨዋታዎችን መርተዋል፡፡ ቪክቶር…

በአፍሪካ ዋንጫ ካሜሮን ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀች

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ካሜሮን ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀቀች። ምሽቱን ለደረጃ የሚደረግ ፍልሚያ በአዘጋጇ ሀገር ካሜሮንና በቡርኪናፋሶ መካከል ተደርጓል። ጨዋታው 3 አቻ በመጠናቀቁ ወደ መለያ ምት ያመራ ሲሆን፥ በመለያ ምት ካሜሮን ቡርኪናፋሶን 5 ለ 3 በመርታት ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች።…

ዛሬ ምሽት ቡርኪናፋሶ እና ካሜሮን ለደረጃ ይጫወታሉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው የፍሪካ ዋንጫ መርሃ ግብር መሠረት ቡርኪና ፋሶ እና አዘጋጇ ካሜሮን ለደረጃ ይፋለማሉ። ጨዋታው ምሽት 4፡00 ላይ በያውንዴ አህመዱ አሂጆ ስቴዲዬም ይካሄዳል። በሌላ በኩል የአፍሪካ ዋንጫ ነገ ፍፃሜውን የሚያገኝ ሲሆን፥ በዕለቱም ግብጽ እና ሴኔጋል ለዋንጫ ይፋለማሉ። ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ…