በልደታ ክ/ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የG+11 የመኖሪያ ቤት ግንበታ በጥራትና በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ተገለፀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ በልደታ ክፍ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የG+11 የመኖሪያ ቤት ግንባታ በተቀመጠለት ጊዜ በጥራትና በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ግንባታው የደረሰበትን ደረጃ ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡
ከንቲባዋ ለግንባታው መጀመር የመሰረት ድንጋይ ከጣሉነት ጊዜ ጀምሮ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ በየወቅቱ በልዩ ሁኔታ ክትትልና ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኙም ተጠቁሟል፡፡
የህንፃው ብዛት አራት ባለ 11 ወለል ሲሆን እያንዳንዳቸው 11 ፎቆች የሚኖሩት መሆኑ ተመላክቶ ከተጀመረ 29 ቀናትን አስቆጥሯል፡፡
ካለምንም እረፍት ግንባታው እየተከናወነ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፥ ለግንባታውም ዘመናዊ ቴክኖሎጅ አገልግሎት ላይ ውሏል ነው የተባለው።
ህንፃው ሲጠናቀቅ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን የቤት ችግር ያቃልላል መባሉን ከአዲስ አበባ ከንቲባ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!