የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት ለ2015 በጀት ከ6 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር በላይ አጸደቀ
የክልሉ ምክርቤት 14ኛ መደበኛ ጉባዔ የክልሉን ሚዲያ የቦርድ አባላት እና ሚዲያውን ለማቋቋም የወጣውን ጨምሮ የተለያዩ የማሻሻያ አዋጆችን በማጽደቅ ተጠናቋል፡፡
በዚህም ምክር ቤቱ÷ የክልሉን የስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ለማቋቋሚያ አዋጅን መልሶ ለማሻሻል የወጣ ረቂቅ አዋጅ፣ የክልሉን የማረሚያ ቤት ኮሚሽን እንደገና ለማቋቋም የወጣ ረቂቅ አዋጅ፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን ለመመዝገብና ለማስተዳደር የወጣ ረቂቅ ላይ ተወያይቶ አጽድቋል።