Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደሮች በጎንደር ከተማ የፋሲል ግንብን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በተለያዩ ሀገራት ኢትዮጵያን የሚወክሉ አምባሳደሮች በጎንደር ከተማ ታሪካዊና ጥንታዊውን የፋሲል ግንብ ጎብኝተዋል።

በጉብኝት መርሐ ግብሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ተሳትፈዋል።

አምባሳደሮቹ በቀጣይ ቱሪስቶች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የተለያዩ ታሪካዊ የመስህብ ስፍራዎች እንዲጎበኙ የማድረግ ስራ እንዲሚያከናውኑ ይጠበቃል።

ለዚህም ያደረጉት ጉብኝት የበለጠ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ነው የተገለጸው፡፡

በሀብታሙ ተ/ስላሴ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.