Fana: At a Speed of Life!

በአቶ ደመቀ መኮንን የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ታንዛኒያ ገባ

 

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ደመቀ መኮንን የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ታንዛኒያ ዳሬ ሰላም ገብቷል።

ልዑኩ ጁሊየስ ኔሬሬ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ የታንዛኒያ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ምባሮክ ኤን ምባርክ፣ በታንዛኒያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሽብሩ ማሞ እና ዲፕሎማቶች አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

ልዑኩ ነገ እና ከነገ በስቲያ በሚካሄደው የአፍሪካ የሰው ሃብት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ታንዛኒያ መግባቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.