አስተዳደሩ በትምህርት ዘርፍ እያከናወነ ያለው ሥራ አበረታች ነው- ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት አሰጣጡን በማዘመን፣ በእውቀትና በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ ለማፍራት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እያከናወናቸው ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገለጹ፡፡
ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጋር በከተማዋ የትምህርት ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡
ከውይይታቸው በኋላም÷ ሚኒስትሩ የከንቲባ ጽሕፈት ቤትን ጎብኝተዋል፡፡