Fana: At a Speed of Life!

የሁለቱ ምክር ቤቶች 6ኛ ዙር 3ኛ አመት የስራ ዘመን የመክፈቻ ስነ -ስርአት ሰኞ ይካሄዳል

 

አዲስ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የህዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች 6ኛ ዙር 3ኛ አመት የስራ ዘመን የመክፈቻ ስነ-ስርአት የፊታችን ሰኞ ይካሄዳል ።

የምክር ቤቱ የህዝብ ግንኝነት ዳይሬክተር አቶ ያቆብ ወልደሰማያት ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት÷ መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ.ም በሚካሄደው የመክፈቻ ስነ- ስርዓት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የምክር ቤቶቹን መከፈት ያበስራሉ።

ከሰዓት በኋላ በሚካሄደው በዚህ የመክፈቻ ስነ- ስርዓት ፕሬዚዳንቷ የመንግስትን የበጀት አመቱን የትኩረት አቅጣጫዎች የሚያመላክት ንግግር ለምክር ቤቱ ያደርጋሉ።

በመክፍቻ ስነ-ስርዓቱ ከምክር ቤቱ አባላት በተጨማሪ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በበላይ ተስፋዬ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.