ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ቻይና ገቡ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2016(ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ቻይና ቤጂንግ ገብተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቆይታቸው ከሚኒስትሮች ልኡኮቻቸው ጋር በመሆን በ3ኛው የቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም ላይም እንደሚሳተፉ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመለክታል::