Fana: At a Speed of Life!

ሺ ጂንፒንግ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የግሪን ቤልት እና ሮድ አካል ሆኖ ሊደገፍ እንደሚችል አረጋገጡ

 

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ከየልዑካን ቡድናቸው ጋር በመሆን በቻይና ታላቁ የሕዝብ አዳራሽ የሁለትዮሽ ውይይት አደረጉ፡፡

በውይይታቸውም÷ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የቻይና ኢንቨስትመንት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እመርታ የሚኖረውን አስተዋፅዖ አንስተዋል፡፡

አክለውም በተለይም በአምስቱ ቁልፍ ምሰሶዎች ማለትም÷ በግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ አይሲቲ፣ ማእድን ልማት እና ቱሪዝም ላይ ተጨማሪ ኢንቨስትመንት እንዲኖር የማበረታቻ ጥሪ አቅርበዋል::

ፕሬዚዳንት ሺ በበኩላቸው÷ ኢትዮጵያ ብሪክስን በመቀላቀሏ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) እንኳን ደስ ያለዎት ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነትም ከሁሉን አቀፍ ፅኑ ግንኙነት ወደ ሁኔታ የማይፈታው ስልታዊ ትብብር እና ወዳጅነት ደረጃ ከፍ ማለቱን በይፋ አብስረዋል::

የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ- ግብርን ያደነቁት ፕሬዚዳንቱ÷ ከቻይናው አረንጓዴ ልማት ፖሊሲ ጋር ተናባቢ በመሆኑ የግሪን ቤልት እና ሮድ አካል ሆኖ ሊደገፍ እንደሚችል አረጋግጠዋል::

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.