የመከላከያ ሠራዊት ቀን በሠላም መጠናቀቁን የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል አስታወቀ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ የተከበረው የመከላከያ ሠራዊት ቀን በሠላም መጠናቀቁን የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል አስታወቀ።
የቀኑን መከበር ተከትሎ ለተሽከርካሪ ዝግ የነበሩ መንገዶች ተከፍተው መደበኛ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡