Fana: At a Speed of Life!

አብርሆት ቤተ-መጻሕፍት የ24 ሰዓት አገልግሎት መስጠት ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አብርሆት ቤተ -መጻሕፍት የሚሰጠውን አገልግሎት ወደ 24 ሰዓት ማሳደጉን አስታውቋል፡፡

የቤተ-መጻሕፍቱ ዋና ዳይሬክተር ውብአየሁ ማሞ(ኢ/ር)÷ቤተ-መጻሕፍቱ ከሕዳር 14 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ምሽቱ ስድስት ሰዓት አገልግሎት ሲሰጥ እንደቆየ አንስተዋል፡፡

ከዛሬው ዕለት ጀምሮም የ24 ሰዓት አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ነው ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት፡፡

የቤተ-መጻሕፍቱ አገልግሎት ፈላጊ ቁጥር የአገልግሎት ሰዓቱን ለማሻሻል ምክንያት እንደሆነም አመላክተዋል።

ቤተ-መጻሕፍቱ በቀን ከ15 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በሌላ በኩል ቁጥር ሁለት የአብርሆት-ቤተ-መጻሕፍት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሊገነባ መሆኑ ተገልጿል።

በሜሮን ሙሉጌታ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.