Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከአሜሪካ አምባሳደር ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መከሩ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ ከአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጆሴ ማሲንጋ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።

በውይይታቸው የጋራ በሆኑ ወቅታዊ፣ ሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና በባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።

በተጨማሪም በትምህርት፣ በአቪዬሽን፣ በንግድ እና በሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ላይ በትብብር መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይም መክረዋል።

በዚህ ወቅት አምባሳደር ምስጋኑ ሀገራቱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበት 120ኛ አመት ምስረታ በዓል መከበር፥ የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እንደሚያስችል ጠቁመዋል፡፡

አምባሳደር ማሲንጋ በበኩላቸው ሁነቱ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ በማጠናከር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሣደግ እንደሚረዳ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.