Fana: At a Speed of Life!

ሰመራ ከተማን በጋራ ለማልማት ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአፋር ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አወል አርባ “ሰመራ ከተማን በጋራ እናልማ“ በሚል መሪ ሐሳብ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብርን አስጀምረዋል፡፡

የክልሉ ኮንስትራክሽን እና ከተማ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመድ ኑር ሳሊም (ኢ/ር)፤ ሰመራ ለቀጣዩ ትውልድ ምቹ እንድትሆን የ1ኛው ዙር የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በክልሉ በጀት መጀመሩን እና በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል፡፡

ለፕሮጀክቱ ማስፈፅሚያ ተጨማሪ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር ማካሄድ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱንም ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል፡፡

ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ የአካባቢው ተወላጆች እና ነዋሪዎች “ሰመራ ከተማን በጋራ እናልማ“ ተብሎ በተዘጋጀው መርሐ-ግብር በንቃት እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ገንዘቡን በቴሌ ብር እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈቱ አካውንቶች ገቢ ማድረግ እንደሚቻልም ጠቁመዋል፡፡

በተጨማሪም በቅርቡ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር (ቴሌቶን) እንደሚካሄድ ነው ያመላከቱት፡፡

የሰመራ-ሎግያ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አብዱ ሙሳ በበኩላቸው፤ ሰመራን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እየተከናወነ ባከለው ሥራ በርካታ የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡

በአሊ ሹምባሕሪ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.