ከ40 ቢሊየን ብር በላይ የጡረታ መዋጮ ተሰበሰበ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የግል ድርጅቶች ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር በተያዘው በጀት ዓመት ከ40 ቢሊየን ብር በላይ የጡረታ መዋጮ ሰበሰበ፡፡
የግል ድርጅቶች ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ድሬዳዋ ዲስትሪክት ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል፡፡
የአስተዳደሩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አባተ ምትኩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት÷ አሁን ላይ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ የግል ድርጅት ሠራተኞች የማህበራዊ ዋስትና አግልገሎት ምዝገባ አድርገዋል፡፡
ከ280 ሺህ በላይ የግል ድርጅቶች ሠራተኞቻቸውን በማስመዝገብ ከ2004 ጀምሮ ከ161 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን ገልጸው÷ በዚህ ዓመት ብቻ ከ40 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን አመልክተዋል።
ለጡረታ የተሰበሰበውን ገንዘብ ለኢንቨስትመንት በማዋል ከ38 ቢሊየን ብር ማትረፉን እና አሁን ላይ ከ63 ሺህ በላይ የግል ድርጅት ሠራተኞች የማህበራዊ ዋስት ጡረታ አበል ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሐርቢ ቡኽ በበኩላቸው÷ የጡረታ አቅድ ሽፋንን የማዘመንና ተደራሽ የማድረግ ስራ ለድህነት ቅነሳና ኢንቨስትመንት መስፋፋት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
አስተዳደሩ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያው በተሟላ መልኩ እንዲተገበር እያበረከተ ያለው ጥረት የሚበረታታ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በተሾመ ኃይሉ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!