አቶ ሙስጠፌ ዜጎች በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በንቃት እንዲሳተፉ ጠየቁ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሃመድ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሐ ግብርን በጅግጅጋ ከተማ አስጀምረዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሕብረተሰቡ በተለያዩ ዘርፎች ያለውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡
የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የኢትዮጵያን የመረዳዳት እና የመተባበር ባህል ይበልጥ የሚያጠናከር ተግባር መሆኑንም አውስተዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ የችግኝ ተከላ፣ የአቅመ ደካማ ወገኖች ድጋፍ፣ የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ፣ ደም ልገሳ፣ ነጻ ሕክምና እና ሌሎች ሰው ተኮር ሥራዎች እንደሚከናወኑ አስገንዝበዋል፡፡
ስለሆነም ዜጎች በዘንድሮው የክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
አቶ ሙስጠፌ ዕለቱን በማስመልከት በጅግጅጋ የችግኝ ተከላና የጽዳት መርሐ ግብር ማከናወናቸውንም የክልሉ አካባቢ ጥበቃና የገጠር መሬት አስተዳደር ቢሮ የአየር ንብረት ለውጥ ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ ሂላል መሃመድ ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡
በመላኩ ገድፍ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!