Fana: At a Speed of Life!

 የብሪክስ ተፅዕኖ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል – ፕሬዚዳንት ፑቲን

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ብሪክስ በዓለም አቀፉ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ እና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ ያለው ተፅዕኖ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል አሉ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን፡፡

17ኛው የብሪክስ ዓመታዊ ጉባኤ በብራዚል ሪዮ ዲ ጄኔሮ መካሄድ ጀምሯል፡፡

በመድረኩ በየነ መረብ መልክዕት ያስተላለፉት ፕሬዚዳንት ፑቲን÷ የደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ ታዳጊ ሀገራትን ያሰባሰበው ብሪክስ ከጊዜ ወደ ጊዜ የአባላቱ ቁጥር አድጓል ብለዋል።

አባል ሀገራቱ የፈጠሩት ስትራቴጂካዊ ትብብር በዓለም አቀፉ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ እና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ በጎ ተፅዕኖ እያሳደረ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

የዓለማችንን 40 በመቶ ኢኮኖሚ የሚሸፍኑት የብሪክስ አባላት በሀገራቸው ገንዘብ የሚያደርጉት የንግድ ልውውጥ እያደገ መምጣቱን ጠቅሰው፤ የሀገራቱን የካፒታል ኢንቨስትመንት የበለጠ ማሳደግ ይገባል ነው ያሉት።

በተጨማሪም በግብርና ምርት ልውውጥ፣ በስፖርት እና ሎጀስቲክስ ዘርፍ የአባል ሀገራቱ ትብብር እያደገ መምጣቱን አመላክተዋል፡፡

የባለብዙ ዋልታ ዓለምን ማረጋገጥ የብሪክስ በየነ መንግስታት ስብስብ ዋና ዓላማ መሆኑንም አስምረውበታል።

በሚኪያስ አየለ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.