Fana: At a Speed of Life!

የአቡ ዳቢ በረራ አየር መንገዱ አፍሪካን ከተቀረው ዓለም ጋር የማስተሳሰር ጥረቱን ያጠናክራል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአቡ ዳቢ በረራ መጀመር አፍሪካን ከተቀረው ዓለም ጋር ለማስተሳሰር የሚደረገውን ጥረት የሚያጠናክር ነው አሉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው።

አየር መንገዱ ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ዋና ከተማ አቡ ዳቢ በትላንትናው ዕለት አዲስ በረራ ጀምሯል።

የአየር መንገዱ የመጀመሪያ ተጓዦች አቡ ዳቢ ዛይድ አየር ማረፊያ ሲደርሱ በአውሮፕላን ማረፊያው እና በኢትሃድ ኤርዌይስ ከፍተኛ አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

አቶ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት÷ አየር መንገዱ አፍሪካን ከተቀረው ዓለም ጋር ለማስተሳሰር አዲስ አበባን እንደ ማዕከል በመጠቀም ወደ ተለያዩ መዳረሻዎች እየበረረ ይገኛል ብለዋል።

የአቡ ዳቢ በረራ መጀመርም ይህንን የሚያጠናክር መሆኑን አንስተው÷ ከኢትሃድ ጋር በመተባበር የተጀመረው የቀጥታ በረራ ለተሳፋሪዎች ምቹ ሁኔታን እንዲሁም ለንግድ እና ባህል ትስስር ትልቅ አቅም የሚፈጥር እንደሆነ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አቡ ዳቢ ያስጀመረው አዲሱ በረራ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ያለውን የበረራ መዳረሻ ወደ አራት ያሳደገ መሆኑም ተመልክቷል።

በዘመን በየነ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.