Fana: At a Speed of Life!

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአንድ ጀንበር 6 ነጥብ 8 ሚሊየን ችግኞች ይተከላሉ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ በአንድ ጀንበር 6 ነጥብ 8 ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል በክልል ደረጃ ዝግጅት ተደርጓል አለ።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በክልሉ 502 ሚሊየን ችግኞች ይተከላሉ።

በዓመቱ ከሚተከሉት ችግኞች መካከል 304 ሚሊየን የፍራፍሬ፣ የቡናና የጥምር ደን ሲሆኑ÷ ቀሪ 198 ሚሊየን ችግኞች ደግሞ ለደን ልማት የሚሆኑ ናቸው ብለዋል።

በዚህም 161 ሺህ 925 ሄክታር መሬት ለመሸፈን ዝግጅት ተደርጎ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በሚከናወነው በአንድ ጀንበር 700 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ክልሉ 6 ነጥብ 8 ሚሊየን ችግኞች ለመትከል ተዘጋጅቷል ነው ያሉት።

በአንድ ጀንበር የተከላ ፕሮግራም 2 ሺህ 486 ሄክታር መሬት ለመሸፈን መታቀዱን አንስተው÷ 1 ነጥብ 3 ሚሊየን የሚሆኑ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፎ ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።

ሕብረተሰቡ የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት በየአካባቢው በነቂስ ወጥቶ በመሳተፍ አሻራውን እንዲያሳርፍ ጥሪ አቅርበዋል።

በአድማሱ አራጋው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.