Fana: At a Speed of Life!

ከ308 ቢሊየን ብር በላይ ግዥ በኤሌክትሮኒክ ሥርዓት…

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በተጠናቀቀው 2017 በጀት ዓመት ከ308 ቢሊየን ብር በላይ ግዥ በኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓት ተፈጽሟል አለ የፌዴራል መንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ እንዳሉት ÷ በበጀት ዓመቱ የመንግሥት ግዥና አስተዳደር ሥርዓትን ዘመናዊ ከማድረግ አንፃር አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል።

በ2017 በጀት ዓመት በ169 የፌዴራል ባለበጀት ተቋማትና 93 ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥርዓት ተግባራዊ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡

በዚህም 308 ነጥብ 75 ቢሊየን ብር በኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓት መፈጸሙን ነው የተናገሩት፡፡

300 ቢሊየን ብሩ በጨረታ እንዲሁም 8 ነጥብ 75 ቢሊየን ብሩ ደግሞ ዋጋ በማቅረብ የግዥ ሒደት መከናወኑንም አብራርተዋል።

በ2016 በጀት ዓመት በኤሌክትሮኒክ ሥርዓት የተከናወነው የመንግስት ግዥ 65 በመቶ ሲሆን÷ በ2017 በጀት ዓመት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓት መፈጸሙን ለኢዜአ ገልጸዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.