የሉዓላዊነት ምልክት የሆነውን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያለልዩነት መደገፍ አለብን – አብን
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሉዓላዊነትና የእድገት ምልክት በመሆኑ መላው ኢትዮጵያውያን ያለልዩነት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ጥሪ አቀረበ፡፡
ንቅናቄው ግድቡን በተመለከተ ባወጣው መግለጫ፥ ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብቷ የመጠቀም መብቷ ለድርድር እንደማይቀርብ በመግለጽ፤ የአባይ ወንዝን በፍትሃዊነት የመጠቀም ሉዓላዊ መብት እንዳላት አጽንኦት ሰጥቷል፡፡
ኢትዮጵያ እንደ ህዳሴ ግድብ ባሉ ፕሮጀክቶች አማካኝነት የምታከናውናቸው የኢነርጂ፣ የግብርና ማዘመንና የኢንዱስትሪ ልማት ስራዎች ህጋዊ ብቻ ሳይሆን ለሀገራዊ እድገትና ቀጣናዊ መረጋጋት አስፈላጊ መሆናቸውን ነው ያስታወቀው፡፡
ግብጽ በዓባይ ውሃ ላይ በምታራምደው ጊዜው ያለፈበት፣ መሰረት የሌለውና ኢፍትሃዊ በሆነ ፍላጎት ምክንያት ኢትዮጵያ ከልማት ተከልክላ ልትቆይ አትችልም ሲል ፓርቲው በመግለጫው አስገንዝቧል፡፡
ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ የምትከተለው አቋም ፍትሃዊ የጋራ ተጠቃሚነትን በሚደግፉ ዓለም አቀፍ ህጎች ላይ የተመሰረተ መሆኑን የጠቆመው መግለጫው፥ ህዳሴ ግድብ የልዩነት ምንጭ ሳይሆን የተፋሰሱን ሀገራት ህዝቦች የሚያስተሳስር ነው ብሏል፡፡
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከውስጣዊ የፖለቲካ ልዩነቶች የተሻገረ የልማት፣ የሉዓላዊነት እና የብሄራዊ ደህንነት ጉዳይ በመሆኑ ግድቡን መጠበቅ የመላው ኢትዮጵያውያን የጋራ ኃላፊነት መሆኑንም አስረድቷል፡፡
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!