ዳንኤል ሌቪ ከቶተንሃም ሆትስፐር ሃላፊነታቸው ለቀቁ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የቶተንሃም ሆትስፐር ሊቀ መንበር ዳንኤል ሌቪ ከሃላፊነት መልቀቃቸውን ክለቡ ይፋ አድርጓል።
ዳንኤል ሌቪ የሰሜን ለንደኑን ክለብ ቶተንሃም ሆትስፐር ለ25 ዓመታት ያገለገሉ ሲሆን÷ ስፐርስ በሌቪ የስልጣን ዘመን ብዙ ለውጦችን አሳይቷል።
የ63 ዓመቱ ዳንኤል ሌቪ በሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሃም በነበራቸው ቆይታ 1 ነጥብ 1 ቢሊየን ፓውንድ ለተጫቾች ዝውውር ወጪ አድርገዋል።
የቀድሞ ሊቀመንበር 12 አሰልጣኞችን በቆይታቸው የቀጠሩ ሲሆን ÷ ሁለት ዋንጫዎችንም አሳክተዋል።
ዳንኤል ሌቪ በቶተንሃም ቆይታቸው በሰሩት ሥራ ኩራት እንደሚሰማቸው ገልጸው ለክለቡ ደጋፊዎች ምስጋና አቅርበዋል።
በወንድማገኝ ጸጋዬ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook WMCC
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!