Fana: At a Speed of Life!

መደመር ተብሎ የተጀመረው የሀገራዊ ዕሳቤ ጉዞ የመደመር መንግሥት ላይ ደርሷል – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መደመር ተብሎ የተጀመረው የሀገራዊ ዕሳቤ ጉዞ ዛሬ የመደመር መንግሥት ላይ ደርሷል አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው ‘የመደመር መንግሥት’ የተሰኘው መጽሐፍ በዛሬው ዕለት ተመርቋል፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በማህበራዊ ትስስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንኳን ደስ ያለዎት ብለዋል፡፡

መደመር ተብሎ የተጀመረው የሀገራዊ ዕሳቤ ጉዞ ዛሬ የመደመር መንግሥት ላይ ደርሷል ሲሉም ተናግረዋል፡፡

በአንድ በኩል እየመሩ፣ እየሠሩ፤ በሌላ በኩል ደግሞ እያጠኑ፣ እየመረመሩ ‘የመደመር መንግሥት’ መጽሐፍን በማበርከታቸውም ምስጋና አቅርበዋል፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.