Fana: At a Speed of Life!

የመሪዎች ጉባኤ ሀገራት ከፉክክር ይልቅ በመተጋገዝ ላይ የተመሰረተ እና አብሮ የማደግ እሴት የሚዳብርበት ነው – አቶ ጌታቸው ረዳ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 24ኛው የኮሜሳ መሪዎች ጉባኤ ሀገራት ከፉክክር ይልቅ በመተጋገዝ ላይ የተመሰረተ እና አብሮ የማደግ እሴት የሚዳብርበት ነው አሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተሳተፉበት 24ኛው የኮሜሳ መሪዎች ጉባኤ በዛሬው ዕለት በኬንያ ናይሮቢ ተካሂዷል።

አቶ ጌታቸው ረዳ የመሪዎች ጉባኤውን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ÷ ጉባኤው ሀገራት ከፉክክር ይልቅ በመተጋገዝ ላይ የተመሰረተ እና አብሮ የማደግ እሴት የሚዳብርበት መሆኑን ተናግረዋል።

በአሁኑ ሰዓት ያለው የዲጂታል ሥርዓት የእሴት ሰንሰለቱን የተሻለ ደረጃ በማድረስ በኩል ሀገራት ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ሁኔታ ለማሳየት የሚያስችሉ ልምዶችን የተለዋወጡበት መድረክ እንደሆነ አንስተዋል።

ኮሜሳ ከተቋቋመ ረጅም ጊዜ የሆነና በአፍሪካ ሀገራት መካከል ሊፈጠር የሚገባውን የንግድ ትስስር ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር ብዙ ርቀት የሄደ ተቋም መሆኑንም ጠቁመዋል።

በአድማሱ አራጋው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.