Fana: At a Speed of Life!

ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 18ኛው ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን በመላ ሀገሪቱ በተለያዩ ሁነቶች መከበር ጀምሯል።

በዓሉ “ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተከበረ የሚገኘው።

የሠንደቅ ዓላማ ቀን አሁን ላይ በኢፌዲሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሪነት በተለያዩ አካባቢዎች በተለያዩ ሥነ ሥርዓቶች መከበር ጀምሯል፡፡

4፡30 ሰዓት ላይም በፌደራል የመንግስት ተቋማት፣ በክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች፣ በመከላከያ ሰራዊት ካምፖች እንዲሁም በኤምባሲዎችና የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ሠንደቅ ዓላማ የመስቀል ሥነ ሥርዓት ይከናወናል።

በተጨማሪም በሠንደቅ ዓላማ ፊት ቃለ መሐላ የመፈጸም መርሐ ግብር እንዲሁም ሌሎች ዝግጅቶች የሚከናወኑ ይሆናል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.