የሳይበር ጥቃትን የመከላከል አቅም ማጠናከር…
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የጀመረውን የሳይበር ጥቃት መከላከል አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት ተመላከተ።
በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የውጭ ግንኙነትና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድና የመጀመሪያውን ሩብ አፈጻጻም ሪፖርት አዳምጧል።
የቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት÷ ኢመደአ ከተቋማት ጋር በትብብር በመሥራት ሜጋ ፕሮጀክቶችንና የፋይናንስ ተቋማትን ከሳይበር ጥቃት መከላለከል እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
ኢመደአ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትእግሥት ሃሚድ በበኩላቸው÷ በሩብ ዓመቱ በተለያዩ ተቋማት መሠረተ ልማቶች 13 ሺህ 443 የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች መደረጋቸውን አንስተው፤ 97 ነጥብ 8 በመቶ መከላከል መቻሉን ተናግረዋል፡፡
የሳይቨር ጥቃቶችን የመከላከል አቅሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱንም አመላክተዋል።