በዓለም አቀፉ የጁገል ቅርስ ጥበቃ ስራ ላይ የኢትዮ ቴሌኮም ዐሻራ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም አቀፉ የጁገል ኮሪደር መልሶ ልማት ስራዎች ላይ ዐሻራውን በማኖር ማሕበራዊ ተሳትፎን አጠናክራለሁ አለ ኢትዮ ቴሌኮም።
በተቋሙ የማዕከላዊ ምስራቅ ሪጅን ኦፕሬሽን ዳይሬክተር አቶ ቸሩ ጅማ እንዳሉት÷ ሪጅኑ በዓለም አቀፉ የጁገል ቅርስ የኮሪደር መልሶ ልማት ስራ በመሳተፍ ዐሻራውን ለማኖር ሳይት ተረክቦ ወደ ስራ ገብቷል።
በክልሉ በኮሪደር ልማት ዘርፍ በተለይ በዓለም አቀፉ የጁገል ቅርስ መልሶ ልማት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸው÷ ኢትዮ ቴሌኮምም ከመደበኛ ስራው በተጨማሪ በተለያዩ ማሕበራዊ ተግባራት ላይ በመሳተፍ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል ነው ያሉት።
በዛሬው ዕለትም ዓለም አቀፉን የጁገል ቅርስ ጠብቆ ለትውልድ ለማስተላለፍ በተጀመረው የጁገል ኮሪደር መልሶ ልማት ስራ በመሳተፍ ዐሻራውን ለማኖር ሳይት ተረክቦ ወደ ስራ መግባቱን ተናግረዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም ማሕበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ማረጋገጣቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ሔኖክ ሙሉነህ ለፋና ዲጂታል ገልጸዋል።
በክልሉ ባህል፣ ቅርስና ቱሪዝም ቢሮ የቅርስ ዳይሬክተር አሚር ረመዳን (ኢ/ር) በበኩላቸው÷ የኢትዮ ቴሌኮም ማዕከላዊ ምስራቅ ሪጅን በዓለም አቀፉ የጁገል ቅርስ ጥበቃ ስራ ላይ በመሳተፍ ላደረገው አስተዋጽዖ ምስጋና አቅርበዋል።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook WMCC
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!