Fana: At a Speed of Life!

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የቀድሞ አፈ ጉባኤ ያለው አባተ ሥርዓተ ቀብር ነገ ይፈጸማል

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፌዴሬሽን ምክር ቤት የቀድሞ አፈ ጉባኤ አምባሳደር ያለው አባተ ሥርዓተ ቀብር በነገው ዕለት ይፈጸማል።

ምክር ቤቱ ለፋና ዲጂታል እንደገለጸው፤ የቀድሞ አፈ ጉባኤ አምባሳደር ያለው አባተ ክብራቸውን የሚመጥን ሥርዓተ ቀብር ለማስፈጸም ኮሚቴ ተቋቁሞ እየሰራ ይገኛል።

በመሆኑም በነገው ዕለት ከመኖሪያ ቤታቸው በማርች ባንድ የታጀበ የአስከሬን ሽኝት ተደርጎ፤ በመንበረ ጸባኦት ቅድስተ ሥላሴ ካቴድራል ቤተክርስትያን ሥርዓተ ቀብሩ ይፈጸማል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የቀድሞ አፈ ጉባኤ አምባሳደር ያለው አባተ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት ሕይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.