Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 54 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ያልተጣራ ትርፍ አገኘ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት 9 ወራት 54 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ያልተጣራ ትርፍ አስመዘገበ፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሶስተኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሂዷል፡፡

የባንኩ ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሃብት መጠን ወደ 2 ነጥብ 87 ትሪሊየን ብር አድጓል።

በዘጠኙ ወራት ከፍተኛ ገቢ መሰብሰቡን ያነሱት ፕሬዚዳንቱ÷ ከገቢው ጋር የሚመጣጠን የወጪ አጠቃቀም ለመተግበር መስራት እንደሚገባ ማስገንዘባቸውን ባንኩ ለፋና ዲጂታል የላከው መረጃ አመላክቷል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.