Fana: At a Speed of Life!

ሜ/ጀ መሰለ መሰረት እና ሜ/ጀ ዘውዱ በላይ ከሰሜን ምዕራብ ዞን ነዋሪዎች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል መሰለ መሰረት እና የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ዘውዱ በላይ ከሰሜን ምዕራብ ዞን ፅምብላ ወረዳ የእንዳባጉና ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ጋር ተወያዩ፡፡
 
ሁለቱ የመከላከያ ከፍተኛ የጦር አዛዦች በጋራ በመሩት በዚህ ስብሰባ ÷የአካባቢው ነዋሪዎች በወቅታዊ ችግሮችና መደረግ ስለሚገባው ጉዳይ ሀሳብና ጥያቄ አቅርበው በአመራሮቹ መልስና ማብራሪያ ተሰጥቷል ።
በትግራይ ክልል በርካታ አካባቢዎች በህዝቡ ላይ ለደረሰውና እየደረሰ ላለው ማህበራዊ ችግር ተጠያቂውና ባለቤቱ ስልጣኑን ብቻ ለማራዘም የተቻለውን ሁሉ ሲሰራ የነበረው የህወሀት ጁንታ መሆኑን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል ፡፡
ነዋሪዎቹ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ስራ ላይ ባለመሆናቸው ህዝቡ ችግር ላይ እንደወደቀ የገለጹ ሲሆን ፣ ለችግሩም መፍትሄ እንዲሰጠውም ጠይቀዋል።
ከህግ ማስከበር ዘመቻው በፊት ህወሀት ለአምባገነን አሰራሩ ይጠቀምበት የነበረውና ህዝብን አንቆ የያዘበት የአንድ ለአምስት አደረጃጀት አልፈረሰም ብሎ የሚያስብ ህዝብ ስላለ አሁንም ፍራቻ እየተፈጠረ እንደሆነም ጠቁመዋል።
አያይዘውም የአካባቢውን ሰላም ለመጠበቅ የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡም አረጋግጠዋል።
ሜጀር ጀነራል መሰለ መሰረት የኢትዮጵያ የሩቅና የቅርብ ጠላቶች ለሀገሪቱ ሁሉን አቀፍ ውድቀት ብዙ እየሰሩ ባሉበት ወቅት ፣ ሀገርን ያለ እረፍት እየጠበቀ ያለውን የመከላከያ ሰራዊት ከጀርባው መውጋቱ ሉአላዊነት ያስደፈረና የሀገርን ጥቅም አሳልፎ የሰጠ እንደሆነ ገልጸዋል።
ሜጀር ጀነራሉ አያይዘውም የጁንታውን የሀገር ሻጭነት ልክና ነውረኛ ተግባር በዝርዝር ለነዋሪዎች አስረድተዋል።
ኢትዮጵያን እንደፈለገ የማተራመስና የማፍረስ የጁንታው ዓላማ በጀግናው የመከላከያ ሰራዊት እስከ መስዕዋትነት የደረሰ ተጋድሎ በአጭር ጊዜ መክሸፉና መደምሰሱን ያብራሩት ሜጀር ጀነራል መሰለ መሠረት ÷ በጁንታው ጉዳት የደረሰባቸው አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ስራ ለማስጀመር የተቀናጀ ስራ እየተሰራ ይገኛልም ነው ያሉት፡፡

ሜጀር ጀነራል   ዘውዱ በላይ በበኩላቸው ÷ሁሉም ነገር የሚስተካከለው በሂደት መሆኑን ጠቁመው÷ተገደውም ይሁን ተሳስተው የጁንታው የጥፋት ተልዕኮ ውስጥ ሆነው እጃቸውን ለሰራዊቱ ያልሰጡ ወጣቶችን ፣ የሀይማኖት አባቶች ፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ወላጆች መክረው እንዲመልሱም ማሳሰባቸውን ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ገጽ ያገኘ ነው መረጃ ያመላክታል።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.