Fana: At a Speed of Life!

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በክልልነት የመደራጀት ህዝበ ውሳኔ ድምፅ እየተሰጠ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በክልልነት የመደራጀት ህዝበ ውሳኔ ድምፅ መስጠት በቦንጋ ከተማ በይፋ ተጀምሯል።

በርካታ የከተማዋ ነዋሪዎች የምርጫ ካርድ በወሰዱባቸው ምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው ድምፅ እየሰጡ ይገኛሉ።

ኢዜአ ባደረገው ምልከታ ድምፅ የመስጠት ሂደቱም ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እየተከናወነ ነው።

የካፋ፣ ሸካ፣ ቤንች-ሸኮ፣ ዳውሮ፣ ምዕራብ ኦሞ ዞኖች እና ኮንታ ልዩ ወረዳ “በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል” ለመደራጀት የሚያካሂዱት ህዝበ ውሳኔ ሲሆን÷ ከ 1 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ ዜጎች ድምፅ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.