Fana: At a Speed of Life!

የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ድምጽ ሰጡ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ከክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሚስራ አብደላ ድምጻቸውን ሰጥተዋል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሯ እና የክልሉ የብልፅግና ፖርቲ ሃላፊ አቶ አብዱልጀባር መሀመድ ጋ በአቦከር የምርጫ ጣቢያ መገኘት ነው ድምፃቸውን የሰጡት።

ወይዘሮ ሚስራ አብደላ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልክት ሁሉም የክልሉ ነዋሪ ህገመንግስታዊ መብቱን በመጠቀም ምርጫውን ማከናወን ይጠበቅበታል ብለዋል።

የክልሉ ብልፅግና ፖርቲ ሃላፊ አቶ አብዱልጀባር መሀመድ በበኩላቸው ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሀረሪ በሰላም እየተካሄደ እንደሚገኝ ገልፀው፣ ምርጫው በሰላም ይጠናቀቅ ዘንድ ህብረተሰቡ እያሳየው ለሚገኘው ትብብር አመስግነዋል።

በእዮናዳብ አንዱዓለም

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.