Fana: At a Speed of Life!

አቶ ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ የምሥራቅ አፍሪካ ልዩ ልዑክ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 9 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ የምሥራቅ አፍሪካ ልዩ ልዑክ ጄፈሪ ፊልትማን ጋር ተወያዩ።
በውይይታቸው ወቅት ከአሸባሪው ህወሓት ጋር የሚደረገው ጦርነት ስለሚቆምበት መንገድ የአሜሪካ ሐሳብ ምን እንደሆነ በልዩ ልዑኩ በኩል የተነሣ ሲሆን፥ አቶ ደመቀም የኢትዮጵያን አቋም አስረድተዋል።
በኮምቦልቻና በላሊበላ ለሰብአዊ እርዳታ የሚውሉ በረራዎች መፈቀዳቸውን አቶ ደመቀ በዚህ ወቅት ገልጸዋል።
ወደ ትግራይም 369 እርዳታ የጫኑ መኪናዎች እንዲገቡ መፈቀዱን ጠቅሰው፥ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገኙ የአሜሪካ ዜጎችን ሁኔታ በተመለከተም ውይይት አድርገዋል።
አሸባሪው ሕወሓት አሁንም ቢሆን በአፋርና በአማራ ክልሎች ጥቃት እየፈጸመና ከፍተኛ ሰብአዊና ኢኮኖሚያዊ ውድመት እንዲሁም ስነልቦናዊ ጉዳት እያደረሰ መሆኑንም አስረድተዋል።
አያይዘውም ከሁለቱ ክልሎች ለቆ እንዲወጣ ግፊት ሊደረግበት እንደሚገባ ማሳሰባቸውን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት መረጃ ያመላክታል።
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
May be an image of text that says '# በኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት FDRE Government Communication Service'
0
People reached
441
Engagements
Distribution score
Boost post
399
24 Comments
18 Shares
Like

 

Comment
Share
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.