Fana: At a Speed of Life!

የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት የተለያዩ ሚኒስትሮች አዲስ አበባ ገቡ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በምታስተናግደው ሁለተኛው የምሥራቅ አፍሪካ የጥበባት እና ባህል ፌስቲቫል ላይ የሚሳተፉ የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት ሚኒስትሮች አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ በዚሁ መሠረት የደቡብ ሱዳን የባህል ሙዚየምና ብሔራዊ ቅርስ ሚኒስትር…

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በሆሳዕና የኮሪደር ልማት ሥራን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በሆሳዕና ከተማ እየተካሔደ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ጎበኙ፡፡ ከርዕሰ መሥተዳድሩ በተጨማሪ በየደረጃው የሚገኙ የክልል እና የሀዲያ ዞን አመራሮች በጉብኝቱ ላይ መሳተፋቸውን…

ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከዩክሬን ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር በስልክ ለአንድ ሠዓት የዘለቀ ስኬታማ ውይይት ማድረጋቸውን ገለጹ፡፡ ውይይቱ የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነትን በሰላም ለመቋጨት በሚደረገው ጥረት በሩሲያ ፕሬዚዳንት ፑቲን…

አምባሳደር ደሚቱ ከዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ ከፍተኛ ኃላፊ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጣሊያን የኢትዮጵያ አምባሳደር ደሚቱ ሃምቢሳ ከዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ ረዳት ምክትል ፕሬዚዳንት እና የፋይናንስ ኦፕሬሽን ዲፓርትመንት ኃላፊ ሀርናን ዳነሪ አልቫራዶ ጋር ተወያዩ፡፡ በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት፣ በአረንጓዴ…

ፕሬዚዳንት ፑቲን የሩሲያ የንግድ ድርጅቶች ከብሪክስ አባል ሀገራት ጋር እንዲተባበሩ አሳሰቡ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሀገራቸው የንግድ ድርጅቶች ከብሪክስ አባል ሀገራት ጋር በትብብር እንዲሠሩ አሳሰቡ፡፡ ፕሬዚዳንቱ በሩሲያ የኢንዱስትሪ እና የሥራ ፈጣሪዎች ኅብረት ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ተቋማቱ በብሪክስ…

ጅቡቲ ለኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት የመስሪያ ቦታ አበረከተች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የጅቡቲ መንግስት በሀገሪቱ ለሚገነባው የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት መስሪያ የሚሆን አራት ሄክታር መሬት በስጦታ አበርክቷል። በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ፥ የመሬት ስጦታው የኢትዮጵያ እና ጅቡቲ መልካም ወዳጅነት ማሳያ መሆኑን…

የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም ዓላማ ህፃናት ጥራት ያለው ትምህርት እንዲደርሳቸው ማድረግ ነው – ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም ዓላማ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ህፃናት ጥራት ያለው ትምህርት እንዲደርሳቸው ማድረግ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናገሩ። ሚኒስትሩ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ከህብረተሰቡ የተነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ…

እየጣለ ያለው ዝናብ ለበልግ አብቃይ አካባቢዎች ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሁኑ ወቅት እየጣለ ያለው ዝናብ ለበልግ አብቃይ አካባቢዎች ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ፈጠነ ተሾመ ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር በነበራቸው ቆይታ÷ኢትዮጵያ ከክረምት…

የጤና አገልግሎትን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው – ዶ/ር መቅደስ ዳባ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የጤና ሥርዓቱን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አዘጋጅነት በጤናው ዘርፍ ከሕብረተሰቡ ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽና…

በኦሮሚያ ክልል 11 ነጥብ 4 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ እንደሚቀርብ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል ለ2017/18 የምርት ዘመን 11 ነጥብ 4 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ እንደሚቀርብ የክልሉ ህብረት ስራ ማህበር ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ የኤጀንሲው ኃላፊ ጀማል ከድር የምርት ዘመኑን የአፈር ማዳበሪያ ስርጭት…