Fana: At a Speed of Life!

የአንበጣ መንጋ የሚያስከትለውን ጉዳት ለመከላከል አቅዶ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከግብርና፣ አርብቶ አደርና አካባቢ ጥበቃ እና ከውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች የተውጣጣው ቡድን በክልሎች ተንቀሳቅሶ የአንባጣ መንጋ ያስከተለውን ጉዳት በመስክ ምልከታ ካረጋገጠ በኋላ ባቀረበው ሪፖርት…

አቶ ደመቀ መኮንን ከኬንያ ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከኬንያ ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር ተወያዩ። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ የቀጠናው ሀገራት መንግስት የጀመረውን…

ጽንፈኛው የህወሓት ቡድን የትግራይ ወጣቶች የተሳሳተ አመለካከት እንዲኖራቸው ሲሰራ መቆየቱን በቁጥጥር ስር የዋሉ የክልሉ ልዩ ኃይል አባላት ተናገሩ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጽንፈኛው የህወሓት ቡድን የትግራይ ወጣቶችን 'እኔ ከሌለሁ መኖር አትችሉም' እያለ የተሳሳተ አመለካከት እንዲኖራቸው ሲሰራ መቆየቱን በቁጥጥር ስር የዋሉ የክልሉ ልዩ ኃይል አባላት ተናገሩ። ከልጅነታቸው ጀምሮ የተሳሳተ አመለካከት ይዘው እንዲያድጉ…

የህወኃት ዘራፊ ቡድን ሀገር ለማተራመስ ሲዘጋጅባቸው የነበሩ የጦር መሳሪያዎች በሁመራ ግንባር ተያዙ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል እና ሚሊሻ የተባበረ ክንድ የጦር ሜዳ መነጽርን ጨምሮ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን መያዛቸውን የ23ኛ ክፍለ ጦር 2ኛ ብርጌድ ምክትል አዛዥ ኮሉኔል አየለ ቢክቱ ቱፋ ገለጹ፡፡  …

በ24 ሰዓታት 336 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ12 ሰዎች ህይወት አልፏል

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገው 4 ሺህ 213 የላብራቶሪ ምርመራ 336 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 103 ሺህ 56 መድረሱንም ሚኒስቴሩ…

ኢትዮጵያና ፈረንሣይ የ15 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያና ፈረንሣይ ለከተሞች የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን መርሃ ግብር የሚውል የ15 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሪት ያስሚን ዎሃብረቢ እና በኢትዮጵያ የፈረንሣይ አምባሳደር ሬሚ ማሬሾ…

አቶ ገዱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተላከ መልዕክት ለጂቡቲው ፕሬዚደንት ኢስማኤል ዑመር ጊሌ አደረሱ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተላከ መልዕክት ለጂቡቲው ፕሬዚደንት ኢስማኤል ዑመር ጊሌ በዛሬው ዕለት አድርሰዋል፡፡ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የኢትዮጵያ ወቅታዊ…