Fana: At a Speed of Life!

የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ለ2015 በጀት አመት ከ3 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ አፀደቀ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 27 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ባካሄደው 6ኛ ዙር 1 አመት 2 መደበኛ ጉባኤ 3 ቢሊየን 405 ሚሊየን 105 ሺህ ብር ሆኖ የቀረበለትን የክልሉ መንግስት የ2015 በጀት አፅድቋል። የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ምክትል ኃላፊ አብዱልባሲጥ…

“ሐላል የምግብና ቱሪዝም ኤክስፖ” የፊታችን ሰኞ እንደሚጀምር ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የ”ሐላል” የምግብና ቱሪዝም ኤክስፖ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡ ኤክስፖው ‘’ከኢድ እስከ ኢድ ጉዞ ወደ ሀገር ቤት’’ የሚለው መርሐ -ግብር አካል መሆኑም ነው የተመለከተው፡፡ ኤክስፖውን በርካታ ቀጥር ያላቸው…

በአውሮፓ የዘለቀው የጋዝ አቅርቦት ቀውስ ከ“ድጡ” ወደ “ማጡ” እየሄደ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ የዘለቀው የኃይል አቅርቦት ቀውስ ከመሻሻል ይልቅ ከ”ድጡ” ወደ “ማጡ” እየሄደ መሆኑን የአሜሪካን ባንክ ጠቅሶ አንድ ግብይት ላይ መረጃዎችን የሚያወጣ ድረ-ገጽ አስነብቧል፡፡ የሩሲያ የነዳጅ ማስተላለፊያ ቱቦዎች በመበላሸታቸው ምክንያት…

የምክክር ሂደቱ በሥኬት እንዲጠናቀቅ የንግዱ ማኅበረሰብ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያውያን የምክክር ሂደት ያለማንም የውጭ ጣልቃ ገብነት በሥኬት እንዲጠናቀቅ የንግዱ ማኅበረሰብ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ። የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ÷ ባለፉት አምሥት ወራት ኮሚሽኑ…

ለሕግ ታራሚዎች ተገቢውን አያያዝ እና የፍትሕ አገልግሎት ማቅረብ እንደሚገባ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕግ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው ተገቢው አያያዝ ማግኘት እንዳለባቸው እና በቆይታቸውም ፍትሕ አግኝተው ታንጸው እንዲወጡ መሥራት እንደሚገባ የፍትሕ ሚኒስትር ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ገለጹ፡፡ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ÷ በቤንሻንጉል ጉሙዝ…

የሥኳር ሕመም ምልክቶች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰዎች ሐኪም ዘንድ ከመቅረባቸው በፊት በሥኳር ሕመም ተይዘው ሊሆን እንደሚችል በሚያሳዩት ምልክቶች ቀድመው ሊገነዘቡ ይችላሉ፡፡ በተደጋጋሚ የሽንት መምጣት፣ ውሃ ጥም፣ ክብደት መቀነስ፣ ተደጋጋሚ የርሃብ ስሜት፣ ብዥ ያለ ዕይታ፣ የእጅ ወይም የእግር…

በጄኔቭ የፀጥታ ማዕከል እና በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ትብብር ሲተገበር የቆየው ፕሮጀክት ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጄኔቭ የፀጥታ ዘርፍ አስተዳደር ማዕከል (DCAF) እና በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ትብብር በልዩ ልዩ ዘርፎች ለሁለት ዓመታት ሲተገበር የነበረው ፕሮጀክት መጠናቀቁ ተገለፀ፡፡ የፀጥታ ዘርፍ ሪፎርምን አስመልክቶ ለፌዴራል ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች…

እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ ሕጻናት በኤድስ እንዳይያዙ ለማረጋገጥ የሚሰራ ዓለም አቀፍ ጥምረት ተመሰረተ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሕፃናት በኤድስ እንዳይያዙ የሚሰራ ዓለም አቀፍ ጥምረት መመስረቱን የዓለም ጤና ድርጅት በይፋዊ ገጹ አስታውቋል፡፡ ጥምረቱ እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ ማንኛውም ሕጻን ከኤድስ ነጻ እንዲሆን የማድረግ ግብ እንዳለው ተጠቁሟል። እስካሁን በዓለም…

ቻይና የናንሲ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት በውስጥ ጉዳዬ ጣልቃ እንደመግባት ይቆጠራል አለች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ወደ ታይዋን የሚያደርጉት ጉዞ በቻይና የውስጥ ጉዳይ እንደመግባት እንደምትቆጥር ቤጂንግ ገለፀች። የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፥ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሺ ጂን ፒንግ አፈ-ጉባዔዋ…

የበለጸጉ ሀገራት የዝንጀሮ ፈንጣጣ ክትባት በቅድሚያ ለማግኘት ሽሚያ ላይ ናቸው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢኮኖሚ የበለጸጉ ሀገራት አፍሪካን በመዘንጋት የዝንጀሮ ፈንጣጣ ክትባትን በቅድሚያ በእጃቸው ለማስገባት ሽሚያ ላይ መናቸው ተገልጿል፡፡ የበለጸጉ ሀገራት በሚሊየን የሚቆጠር የዝንጀሮ ፈንጣጣ ክትባት ለመግዛት እየጠየቁ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡…