Fana: At a Speed of Life!

የመዲናዋ ወጣቶች የጥምቀት በዓል የሚከበርበትን ጃን ሜዳ አጸዱ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ለጥምቀት በዓል የበርካታ ታቦታት ማደሪያ የሆነውን የጃን ሜዳ አካባቢ ማጽዳታቸውን የከተማ አስተዳደሩ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስታውቋል፡፡ በጽዳት መርሐ-ግብሩ ከ2 ሺህ በላይ ወጣቶች፣ የስፖርት ቤተሰቦች፣ የሃይማኖት…

ከጣሊያን ጋር የተፈረመውን የክህሎት መሰረተ ልማት ግንባታ ስምምነት ለመተግበር የሚያስችል ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያና ጣሊያን መንግስት መካከል የተፈረመውን የክህሎት መሰረተ ልማት ግንባታ ስምምነት ወደ ትግበራ ለማስገባት የሚያስችል ውይይት ተካሄደ። የሥራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ ስምምነቱን ወደ ትግበራ ማስገባት…

የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት 16 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ገቢ ሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ባለፉት 6 ወራት ከተለያዩ አገልግሎቶች 16 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታውቋል፡፡ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በሰጡት መግለጫ ባለፉት 6 ወራት 10 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ…

የፋሲለደስ እድሳትና የጎንደር ኮሪደር ልማት ሥራ እድገት እጅግ አበረታች ነው – ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጎንደር ከተማ እየተካሄዱ ያሉት የፋሲለደስ እድሳት እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች እድገት እጅግ አበረታች ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በጎንደር ከተማ እየተካሄዱ ያሉ የፋሲለደስ እድሳት…

በባቱ የጥምቀት በዓልን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት ተጠናቅቋል

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ባቱ ከተማ የጥምቀት በዓልን በድምቀት ለማክበር አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን የኦሮሚያ ክልል ቱሪዝም ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ የኮሚሽኑ ም/ ኮሚሽነር አቶ ነጋ ወዳጆ እንዳሉት፥ በከተማው የጥምቀት በዓል ሃይማኖታዊ…

የነዳጅና ሸቀጦች አስተማማኝ አቅርቦት እንዲቀጥል መንግስት ከፍተኛ ድጎማ አድርጓል – አቶ አሕመድ ሽዴ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ነዳጅን ጨምሮ ስትራቴጂክ የሚባሉ ሸቀጦች አስተማማኝ አቅርቦት እንዲኖራቸው መንግስት ከፍተኛ ድጎማ ማድረጉን የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ ገለጹ፡፡ አቶ አሕመድ ሽዴ እንዳሉት መንግስት ባለፉት ዓመታት ከ267 ቢሊየን ብር ለነዳጅ ድጎማ ያደረገ…

እስራኤልና ሃማስ በዚህ ሳምንት የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ይደርሳሉ ተባለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5/.2017 (ኤፍ ኤም ሲ) እስራኤልና ሃማስ በተያዘው ሳምንት የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንደሚደርሱ የአሜሪካ የብሔራዊ ጸጥታ አማካሪ ጄክ ሱሊቫን ገለጹ። የጸጥታ አማካሪው ዛሬ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ÷ሁለቱ ወገኖች የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለመፈረም ጫፍ…

ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ከዴንማርክ ልዕልት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከዴንማርክ ልዕልት ቤኔዲክቴ አስትሪድ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በሕጻናት ድጋፍና ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ በጋራ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡

ጀርመን የኢትዮጵያ ታዳሽ የሃይል ልማት ሥራ አበረታች መሆኑን ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ሀንስ ሃንፊልድ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት÷ኢትዮጵያ ንጹህ የአረንጓዴ ኢነርጂ በማምረት ቀጣናውን በሃይል ለማስተሳሰር እየሰራች መሆኑን…

ከ160 በላይ ዜጎች ከቤሩት ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በቤሩት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የቆዩ ከ160 በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡ ተመላሾቹ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት የሥራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።…