Fana: At a Speed of Life!

2 ሺህ ካሬ ሜትር ይዞታ ለማሰጠት በሚል ከ8 ማሊየን ብር በላይ በማታለል የወሰዱ ጥፋተኛ ተባሉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 2 ሺህ ካሬ ሜትር ይዞታ ለማሰጠት በሚል ከ8 ማሊየን ብር በላይ ከግለሰብ በማታለል ወስደዋል የተባሉ ተከሳሾች ጥፋተኛ ተባሉ። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4 ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በከባድ ማታለል ሙስና ወንጀል የተከሰሱትን…

ሔር ኢሴ ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሶማሌ ዒሳ ማህበረሰብ ያልተጻፈ ባሕላዊ ሕግ “ሔር ኢሴ” ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት በድሬዳዋ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ በውይይት መድረኩ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳን ጨምሮ የሶማሊያ እና የጅቡቲ ባህልና ቱሪዝም የሥራ ሃላፊዎች እና ሌሎች…

ሔር ኢሴ የኢትዮጵያ፣ ሶማሊያና ጅቡቲን የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር እንደሚያጠናክር ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሶማሌ ዒሳ ማህበረሰብ ያልተጻፈ ባሕላዊ ሕግ “ሔር ኢሴ” የኢትዮጵያ፣ ሶማሊያና ጅቡቲን የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር እና ወንድማማችነት እንደሚያጠናክር ተገልጿል፡፡ “ሔር ኢሴ” በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) የሰው…

በወሊሶ ለሚገነባው ልዩ አዳሪ ት/ቤት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ

አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በወሊሶ ከተማ ለሚገነባው ልዩ አደሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠዋል። ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ብቁ፣ ተወዳዳሪና ለወደፊት ለሀገሪቱ ጠንካራ መሪ ለማውጣት ግብዓት…

በኦሮሚያ ክልል የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ዘመቻ መጀመሩን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡ በመርሐ ግብሩ 3 ነጥብ 3 ሚሊየን ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ለማከናወን መታቀዱን ተመላክቷል፡፡ በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የአፈርና ውሃ…

4 ሺህ 392 ካሬ ሜትር ይዞታ ለግለሰቦች እንዲሰጥ በማድረግ ወንጀል የተከሰሱ ጥፋተኛ ተባሉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት 4 ሺህ 392 ካሬ ሜትር ይዞታ ያለአግባብ ለግለሰቦች እንዲሰጥ በማድረግና ይዞታውን በመውሰድ ከ132 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት በማድረስ በሙስና ወንጀል የተከሰሱ 48 ግለሰቦች ላይ…

በመዲናዋ ከ800 ሺህ በላይ ተማሪዎች የምገባ አገልግሎት እያገኙ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ ከ800 ሺህ በላይ ተማሪዎች የምገባ አገልግሎት እያገኙ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ምገባ ኤጀንሲ አስታውቋል። የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሽታዬ መሃመድ እንደገለጹት÷ የምገባ አገልግሎቱ ተማሪዎች…

ታጣቂዎች ለተከተሉት ትክክለኛ የሰላም መንገድ ምስጋና ይገባል – አባ ገዳዎች

አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ልዩነትን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሰላም አማራጭን ተቀብለው ለገቡ ታጣቂዎች አባ ገዳዎች ምስጋና አቀረቡ። በክልሉ ይንቀሳቀሱ ለነበሩና የሰላም አማራጭን ለተቀበሉ ታጣቂዎች እውቅና እና ምስጋና የሚያቀርብ መርሐ-ግብ…

ኔዘርላንድስ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር እንደምታጠናክር ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኔዘርላንድስ በተለያዩ ዘርፎች ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከረ ቁርጠኛ መሆኗን ገልጻለች፡፡ የገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከኔዘርላንድስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ስቲጅን ጃንሰን ጋር…

ከሕዳሴ ግድብ 1 ሺህ 950 ቶን የዓሣ ምርት ተገኘ

አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሰው ሠራሽ ሐይቅ 1 ሺህ 950 ቶን የዓሣ ምርት መገኘቱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው የእንስሳትና ዓሣ ሃብት ልማት ዳይሬክተር አቶ ሃይሉ ይርጋ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት፥ ባለፉት 6…