Fana: At a Speed of Life!

የሰላም ኮንፈረንስና ግንኙነት መድረክ በአፋር ክልል እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልል ዞን 5 ሰሙ ሮቢ ወረዳና የአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቀወት ወረዳ የሰላም ኮንፈረንስና ግንኙነት መድረክ በአፋር ክልል በኮማሜ ከተማ እየተካሄደ ነው። በሁለቱ ህዝቦች መካከል ከግጦሽና በዕለት ግጭቶች ልዩነቶች ይስተዋሉ እንደነበር…

ዳያስፖራው በቴክኖሎጂ ዘርፍ ባለው ልምድና እውቀት ሀገሩን እንዲደግፍ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ታላቁን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ጥሪን ተቀብለው ወደ ሀገራቸው የመጡ ዳያስፖራዎች ሀገራቸውን በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዘርፍ እንዲደግፉ ጥሪ አቅርቧል። ሚኒስቴሩ ዳያስፖራዎች በዘርፉ ሀገራቸውን ለመደገፍ እና…

በወዳጅነት ፓርክ የባዛር፣ ኤግዚቢሽንና የሙዚቃ ኮንሰርት የመክፈቻ መርሀ ግብር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከታላቁ ጉዞ ወደ ሀገር ቤት ጋር በተያያዘ በወዳጅነት ፓርክ አደባባይ ባዛር፣ ኤግዚቢሽንና የሙዚቃ ኮንሰርት የመክፈቻ መርሀ ግብር እየተካሄደ ነው፡፡ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ገብረ መስቀል ጫላ ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ነሲሴ ጫሊ፣…

በኦሮሚያ ክልል ከ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት የተፋሰስ ልማት ሊከናወን ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ከ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት ላይ የተፋሰስ ልማት ስራ ሊከናወን መሆኑ ተገለጸ፡፡ መርሃ ግብሩ ጥር 6 በአስር ዞኖች እና በ56 ወረዳዎች ይጀመራል የተባለ ሲሆን፥ የተፋሰስ ልማት ሥራው አርብቶ አደሮችን፣ አርሶ አደሮችን…

ዳያስፖራው ለኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅም በትጋት መስራት ይጠበቅበታል – ዶ/ር መሐመድ እንድሪስ

አዲስ አበባ፣ ጥር 2 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዳያስፖራው ማህበረሰብ ኢትዮጵያ ሁልጊዜም በህልውና ትግል ላይ መሆኗን በማሰብ፥ ለአገራዊ ዘላቂ ጥቅም በትጋት መስራት እንዳለበት የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጄንሲ ምክትል ዳይሬክተር ዶክተር መሐመድ እንድሪስ አሳሰቡ። ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ የተባበረ…

በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት ከዳያስፖራዎች ጋር ውይይት እየተደረገ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት ከዳያስፖራው ጋር ውይይት እየተደረገ ነው። ውይይቱ አሸባሪው የህወሓት ወራሪ ቡድን ጉዳት ባደረሰባቸው የአማራ እና የአፋር ክልል አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት የሚረዳ ምክክር በስካይ ላይት ሆቴል…

በክልሉ በተከሰተው ድርቅ ሰውና እንሰሳት እንዳይጎዱ በስፋት እየተሰራ ነው – የሶማሌ ክልል መንግሥት

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በክልሉ በተከሰተው ድርቅ በሰውና በእንሰሳት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ለማድረግ በስፋት እየተሰራ እንደሚገኝ የሶማሌ ክልል መንግሥት አስታወቀ፡፡ የሶማሌ ክልል መንግሥት ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር በክልሉ አከባቢዎች የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ ፥…

የተወሰኑ ሰዎች ክስ መቋረጥ በአውደ ውጊያ ያገኘነው ድል በሰላሙ መድረክም እንዲደገም የሚያግዝ ነው – ጠ/ሚ ዐቢይ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዘላቂ ድል ለማረጋገጥ በጀግንነት ተዋግቶ ህይወትን ገብሮ ማሸነፍ ብቻ ሳይሆን ከእኔ ይቅር ብሎ ለተሸናፊ ይቅርታን መስጠት የአባቶቻችን ታሪክ መሆኑን ማስታወስ እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት የመከላከያ…

ወደር የሌለው የጥቁር አንበሳ ጀግና ሜዳይና የአደዋ ድል ጀግና ከፍተኛ ሜዳይ ለተለያዩ ወታደራዊ መሪዎች ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ወደር የሌለው የጥቁር አንበሳ ጀግና ሜዳይና የአደዋ ድል ጀግና ከፍተኛ ሜዳይ ለተለያዩ ወታደራዊ መሪዎች ተሰጠ፡፡ በዚህም መሰረት ፡- ወደር የሌለው የጥቁር አንበሳ ጀግና ሜዳይ በጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ…

በውስጥና በውጭ የተከፈቱብንን ጦርነቶች በድል የመወጣት አኩሪ ታሪካችን የሚደገምበት የታሪክ አውድ ውስጥ ነን – ዶክተር አብርሃም በላይ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊያን በየዘመናቱ በግልጽ በውጭና በውስጥ ሃይሎች የተከፈቱብንን ጦርነቶች አሳልፈን በመስዋዕት አገርን ያቆየን አኩሪ ታሪክ ያለን ህዝቦች ነን አሉ የኢፌዴሪ የመከላከያ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ። ሚኒስትሩ ይህን ያሉት የመከላከያ…