Fana: At a Speed of Life!

ያሉንን የተፈጥሮ ጸጋዎች ወደ ልማት ለመቀየር በትኩረት ይሰራል – አቶ እንዳሻው ጣሰው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ያሉንን የተፈጥሮ ጸጋዎች ወደ ልማት በመቀየር ድህነትን ታሪክ ለማድረግ በትኩረት ይሰራል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገለጹ፡፡ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው በሀዲያ ዞን ጊቤ ወረዳ የሀንዶሼ አነስተኛ መስኖ…

በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 44 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር ቤት ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መንግስት ከታንዛኒያ የኢሚግሬሽን ኮሚሽን ጋር በመተባበር በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ የነበሩ 44 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ ማድረጉ ተገለጸ፡፡ ፍልሰተኞቹ ከእስር ተፈትተው የጉዞ ሰነድ በማዘጋጀት ዛሬ የመጀመሪያ…

ሩሲያና ቬትናም ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ቃል ገቡ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያና ቬትናም ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ቃል መግባታቸው ተገልጿል፡፡ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለይፋዊ ጉብኝት ቬትናም መግባታቸው ይታወቃል፡፡ ቭላድሚር ፑቲን እና አቻቸው የቬትናም ፕሬዚዳንት ቶ ላም በቬትናም ዋና ከተማ ሃኖይ…

በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 17 ሺህ በላይ ጥይት ተያዘ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰሜን ምሰራቅ ዕዝ ክፍለ ጦር ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት ጋር በቅንጅት ባደረገው ፍተሻ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 17 ሺህ 350 ጥይት መያዙን አስታወቀ። የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አንድ ኮር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ጣሂር…

በሕንድ በተበከለ የአልኮል መጠጥ ምክንያት ብዙዎች ለህልፈት ተዳረጉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡባዊ ሕንድ ታሚል ናዱ ግዛት የተበከለ የአልኮል መጠጥ በመጠጣታቸው ቢያንስ የ34 ሰዎች ህይዎት ማለፉ ተሰምቷል፡፡ በክስተቱ ለህልፈት ከተዳረጉት በተጨማሪ ከ100 የሚልቁ ሰዎችም በአጣዳፊ ተቅማጥ፣ ትውከት እና ከፍተኛ የሆድ ህመም ለሆስፒታል…

ኢትዮጵያዊቷ መቅደስ በማርኔሊ ቤንድ በመሽከርከር ያሳየችው ትርዒት የዓለም ክብረ ወሰን በመሆን ተመዘገበ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊቷ መቅደስ ከበደ ከወገቧ ታጥፋ (ማርኔሊ ቤንድ) ተሸከርካሪ ቁስን በጥርሷ ነክሳ በመያዝ ለአንድ ደቂቃ በመሽከርከር ያሳየችው ትርዒት የዓለም ክብረ ወሰን በመሆን በጊነስ ወርልድ ሪከርድስ መዝገብ ሰፈረ፡፡ ማሪኒሊ ቤንድ ጭንቅላታቸውን ከስር…

ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገራት የጀስቲስ ፎረም ላይ እየተሳተፈች ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት የሚመራ ልዑክ ቡድን ሩሲያ በሚካሄደው የብሪክስ አባል ሀገራት የጀስቲስ ፎረም ላይ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ በሩሲያ ሶቺ ከተማ ትናንት መካሄድ የጀመረው ፎረሙ እስከ ሰኔ 14 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚቀጥል…

ም/ ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የእምነበረድና የቀርከሃ ፋብሪካዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የእምነበረድና የቀርከሃ ፋብሪካዎችን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሐሰን፣ የማዕድን ሚኒስትር ሐብታሙ ተገኝ(ኢ/ር) ና ሌሎችም የመንግሥት…

ጤና ሚኒስቴር እና ግሎባል ፈንድ ከ25 ቢሊየን ብር በላይ የድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጤና ሚኒስቴር እና ግሎባል ፈንድ የቲቪ፣ የኤች አይ ቪ እና የወባ በሽታዎችን መቆጣጠር የሚያስችል ከ25 ቢሊየን ብር በላይ የድጋፍ ስምምነት ተፈራረመዋል፡፡ ስምምነቱን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እና በግሎባል ፈንድ የአፍሪካ ዲፓርትመንት…

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የመቐለ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት አገልግሎት መስጠት ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የመቐለ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተገለጸ። ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ዛሬ መሆኑን ከአገልግሎቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ በዚህም በጊዜያዊነት የጀመራቸው…