Fana: At a Speed of Life!

ፈረንሳይ ከፓሪሱ ኦሊምፒክ በፊት ተኩስ አቁም እንዲደረግ ለሩሲያ ጥያቄ ልታቀርብ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ፈረንሳይ ከፓሪሱ ኦሊምፒክ ቀደም ብሎ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ለሩሲያ ጥያቄ ልታቀርብ መሆኑን ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን አስታወቁ፡፡ የ2024ቱ የፓሪስ ኦሊምፒክ ከፈረንጆቹ ሐምሌ 26 እስከ ነሐሴ 11 በፈረንሳይ ይካሄዳል፡፡ ይህን ተከትሎም…

አትሌት ጀማል ይመር የራሱን ፈጣን ሠዓት በማስመዝገብ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ኮሪያ በተካሄደው የሴዑል ማራቶን አትሌት ጀማል ይመር የራሱን ፈጣን ሠዓት በማስመዝገብ አሸንፏል፡፡ አትሌት ጀማል ውድድሩን ያሸነፈው 2 ሰዓት ከ 6 ደቂቃ ከ8 ሰከንድ በመግባት ሲሆን÷ ይህም የግሉ ፈጣን ሠዓት ሆኖ ተመዝገቧል፡፡

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ከሞሪታንያ ኢስላሚክ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት የተላከላቸውን መልዕክት ተቀበሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሞሪታንያ ኢስላሚክ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሞሃመድ ኦልድ ቼክ ኤል ጋዙዋን የተላከላቸውን መልዕክት ተቀበሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ ከሞሪታንያ ኢስላሚክ ሪፐብሊክ የውጭ…

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የጸጥታ ተቋማት የዓድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ አክሲዮን ማህበር አባል እንዲሆኑ ጥሪ አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የፌዴራል የፀጥታ ተቋማት የዓድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ አክሲዮን ማህበር አባል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የዓድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ የአክሲዮን ድርሻ…

የዩሮፓ ሊግ የሩብ ፍፃሜ ድልድል ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2023/24 የዩሮፓ ሊግ የሩብ ፍፃሜ ድልድል ይፋ ሆኗል፡፡ በድልድሉ መሠረትም ኤሲ ሚላን ከሮማ የሚፋለሙ ይሆናል፡፡ እንዲሁም ሊቨርፑል ከአታላንታ÷ ባየርሊቨርኩሰን ከዌስትሃም ዩናይትድ  ጋር ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡ በሌላ በኩል…

የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ ድልድል ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ ድልድል ይፋ ሆኗል፡፡ በዚሁ መሠረትም አርሰናል ከባየርን ሙኒክ ጋር የሚገናኙ ይሆናል፡፡ እንዲሁም አትሌቲኮ ማድሪድ ከቦርሲያ ዶርትመንድ፤ ሪያል ማድሪድ ደግሞ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ተድልድለዋል፡፡…

በሁዋዌ የአይሲቲ አህጉራዊ ውድድር ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች 3ኛ ደረጃን ያዙ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በተኒዚያ በተካሄደው የሁዋዌ የአይሲቲ ክፍለ አህጉራዊ ፍጻሜ ውድድር ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል። በ”ኮምፒውቲንግ ትራክ” በተደረገው ውድድር ከኢትዮጵያ፣ ማሊ፣ ካሜሩን፣ ሴኔጋል፣ አልጄሪያ፣ ቱኒዚያ፣ ሊቢያ፣ ግብፅ እና…

አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ከካናዳ ፓርላማ ጸሃፊ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በካናዳ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የፓርላማ ጸሃፊ ሮበርት ኦሊፋንት ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸው አምባሳደር ታዬ÷ ካናዳ በአስቸጋሪ ጊዜያት  ለኢትዮጵያ  እያደረገች ያለውን ዘርፈ ብዙ  ድጋፍ አድንቀው…

ጋቪ የክትባት ሽፋንን ለማሳደግ የቁሳቁስ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለፀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ዓለም አቀፉ የክትባቶች ጥምረት (ጋቪ) በኢትዮጵያ የክትባት ሽፋንን ለማሳደግ የሚያስችል የቁሳቁስ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለፀ፡፡ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ከጋቪ ዋና የሀገራት ዳይሬክተር ቶኩንቦ ኦሺን (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል፡፡…

በግራንድ አፍሪካን ራን ለሚሳተፉ አትሌቶች የመኪና ሽልማት ተዘጋጀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሜሪካ ዋሽንገተን ዲሲ በሚካሄደው የግራንድ አፍሪካ ራን ለሚሳተፉ አትሌቶች የመኪና ሽልማት መዘጋጀቱ ተገለፀ፡፡ ግራንድ አፍሪካን ራን በየአመቱ ጥቅምት በገባ በሁለተኛዉ ቅዳሜ በዋሺንግተን ዲሲ ከተማ የሚደረግ የ5 ኪሎሜትር የሩጫ ዉድድር ነዉ።…