Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል 2ኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በጌሌ ተራራ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ጉራዋ ወረዳ ጌሌ ተራራ ላይ ተጀምሯል፡፡ በመርሐ ግብሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰዓዳ አብዱረሀማን…

በጃፖን የሚገኙ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ለመሳተፍ ፍላጎታቸውን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጃፖን የመንግስት እና የግል ኩባንያ ኃላፊዎች  በኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ለመሳተፍ ያላቸውን ፍላጎት ገለጹ፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ከጃፓን የመንግስት እና የግል ኩባንያ የሥራ ኃላፊዎች በኢኖቬሽን እና…

በሻምበል አበበ ቢቂላ መታሰቢያ የማራቶን ውድድር አትሌት ብርሃኑ ነበበው እና ጠጅቱ ስዩም አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ39ኛው የሻምበል አበበ ቢቂላ መታሰቢያ ማራቶን ውድድር አትሌት ብርሃኑ ነበበው እና አትሌት ጠጅቱ ስዩም አሸነፉ። 39ኛው የሻምበል አበበ ቢቂላ መታሰቢያ የማራቶን ውድድር በአዲስ አበባ ከተማ ሰሚት ለስላሳ ፋብሪካ ተብሎ የሚጠራው ቦታ መነሻና…

በተለያዩ አካባቢዎች ለጥፋት ዓላማ ሊውል የነበረ የጦር መሣሪያ በቁጥጥር ስር ዋለ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጃዊ ወረዳ እና በማዕከላዊጎንደር ዞን ሳንጃ ኬላ ለጥፋት ዓላማ ሊውል የነበረ የጦር መሣሪያ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ፡፡ በጃዊ ወረዳ ፈንድቃ ከተማ በሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች ለጥፋት ዓላማ ሊውል የነበረ 98 ፋልኮን ቱርክ ሰራሽ ሸጉጥ፣ 2 ክላሽን…

የአርቲስት ዓሊ ብራ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የተገነባው የክብር ዶክተር አርቲስት ዓሊ ብራ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ፡፡ በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር…

በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የ2ኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የሁለተኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው፡፡ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ሁለተኛውን ዙር የአንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በሰሜን ሸዋ…

አቶ ደመቀ መኮንን ድሬዳዋ ገቡ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ዛሬ ድሬዳዋ ገብተዋል፡፡ ከአቶ ደመቀ መኮንን ጋር የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች ድሬዳዋ ከተማ ገብተዋል፡፡…

ዘላቂ ሰላም እና ልማትን ለማረጋገጥ ለወጣቶች ትኩረት መስጠት ይገባል – ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀገራችንን ዘላቂ ሰላም እና ልማት ለማረጋገጥ ለወጣቶች ትኩረት መስጠት ይገባል ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ የ2015 ዓ.ም የወጣቶች የክረምት በጎ ፈቃድና የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር…

39ኛው የሻምበል አበበ ቢቂላ የማራቶን ውድድር የፊታችን እሁድ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 39ኛው የሻምበል አበበ ቢቂላ የማራቶን ውድድር ሰኔ 18 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡ መነሻ  እና መድረሻውን  ሰሚት  በሚያደርገው የማራቶን ውድድር ÷ 12 ክለቦች፣ 2 ክልሎችና 1 ከተማ…

ዩክሬን ወደ ክሬሚያ በሚወስደው ድልድይ ላይ ጥቃት መፈፀሟን ሩሲያ ገለፀች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዩክሬን ወደ ክሬሚያ በሚወስደው የኮንሃር ድልድይ ላይ የሚሳኤል ጥቃት መፈፀሟን ሩሲያ ገልፃለች፡፡ “የክሬሚያ መግቢያ” በመባል የሚታወቀው ይህ ድልድይ ክሬሚያን ከሩሲያ እና ከደቡባዊ የኬርሰን ግዛት ጋር የሚያገናኝ ሲሆን በድልድዩ ላይ በተፈጸመው…