Fana: At a Speed of Life!

በአዲሱ አመት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች ይከናወናሉ- ከንቲባ ከድር ጁሃር 

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2015 በጀት ዓመት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና የከተማዋን እድገት የሚያንፀባርቁ የልማት ስራዎች ይከናወናሉ ሲሉ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናግረዋል፡፡ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ለ2015 አዲስ ዓመት…

በአዲሱ አመት በክልሉ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በትኩረት ይሠራል – አቶ ኡሞድ ኡጁሉ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋምቤላ ክልል ያለው ሰላም ዘላቂነት እንዲኖረው በአዲሱ ዓመት የክልሉ መንግሥት በትኩረት ይሠራል ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ ገለፁ። አቶ ኡሞድ አዲሱን ዓመት በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ርዕሰ…

ኢትዮ – ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ በተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞች የማበረታቻ ሽልማት አበርክቷል።   

በስካይ ላይት ሆቴል በተካሄደው የሽልማት መርሐ ግብር ላይ አመርቂ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞች እንዳስመዘገቡት ውጤት ከአምስት ሺህ እስከ 300 ሺህ ብር የሚደርስ የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የኢትዮ - ኤሌክትሪክ አትሌት የሆነችውና በ18ኛው የኦሪገን የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች…

ፋሲል ከነማ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታውን ከቡሩንዲው ቡማሙሩ ጋር ዛሬ ያደርጋል

አዲስ አበባ ፣ ጳጉሜን 4 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ፋሲል ከነማ የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታውን ከብሩንዲው ቡማሙሩ ጋር ዛሬ ያደርጋል፡፡ የሁለቱ ክለቦች የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የቅድመ ማጣሪያ በባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ከቀኑ 9 ሰአት ላይ የሚደረግ ይሆናል።…

የጤና ሚኒስቴር ያሰባሰበውን የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ለአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስረከበ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማትና ሠራተኞቹ ያሰባሰበውን የትምህርት ቁሳቁስ ለአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስረከበ። ድጋፉን ያስረከቡት የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ÷ ይህኛው ድጋፍ የበፊቶቹ ጊዜያትድጋፎች አንዱ አካል መሆኑን ገልጸዋል፡፡…

25 ተቋማት በ“ኦንላይን” አገልግሎት እየሰጡ ነው

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) 25 ተቋማት 326 የአገልግሎት ዘርፎችን በ“ኦንላይን” እየሰጡ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር  አስታወቀ፡፡ በሚኒስቴሩ የኤሌክትሮኒክስ አገልግሎት ካለማላቸው ተቋማት ጋር የ”አገልግሎት ቀን” አከባበርን በማስመልከት ተወያይቷል።…

2 ዞኖች ለመከላከያ ሠራዊት ከ47 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው ድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀዲያ እና ደቡብ ጎንደር ዞኖች ለመከላከያ ሠራዊት ከ47 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው የአይነት ድጋፍ አደረጉ፡፡ የሀዲያ ዞን ሕዝብና አስተዳደር 42 ሚሊየን 131 ሺህ ብር ብር ግምት ያላቸው÷ 350 ሰንጋ፣ 542 ፍየልና በግ…

የጉራጌ  እና የጎፋ ዞኖች ለሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰንጋ ድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጉራጌ  እና የጎፋ ዞኖች ለሀገር መከላከያ ሰራዊት 626 የእርድ ሰንጋ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ የጉራጌ ዞን የብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ክፍሌ ለማ ÷ አሸባሪው ህወሓትን  ለመደምሰስ በሚደረገው ጥረት የዞኑ ህዝብ ከመከላከያ ሰራዊት ጎን…

መቻቻል፣ መከባባር ፣ መማማርና እውቀት የሰላም ምንጮች  ናቸው -ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)መቻቻል፣ መከባባር ፣ መማማርና እውቀት የሰላም ምንጮች  ናቸው ሲሉ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ ገለጹ፡፡ ዛሬ ሀገር አቀፍ የሰላም ቀን "ሰላም ለኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል  እየተከበረ ነው፡፡ ቀኑን አስመልክቶ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ፣…

አቶ ብናልፍ አንዷለም ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ሰላም እንዲሰሩ ጥሪ አቀረቡ

አዲስ አበባ ፣ ጳጉሜን 3 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን ሰላም ለእድገትና ብልጽግና ያለውን ዋጋ በመረዳት ለሀገራቸው ሰላም እንዲሰሩ የሰላም ሚኒስትሩ ብናልፍ አንዷለም ጥሪ አቀረቡ። ጳጉሜን 3 የሰላም ቀንን አስመልክቶ የሰላም ሚኒስቴር መግለጫ ሰጥቷል፡፡ መግለጫውን የሰጡት ሚኒስትሩ…