Fana: At a Speed of Life!

የህግ ታራሚዋን አስገድዶ የደፈረው ፖሊስ በዘጠኝ ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የህግ ታራሚዋን በመድፈር የተከሰሰው ፖሊስ በዘጠኝ ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የምዕራብ ሀረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወሰነ። ፍድር ቤቱ ትናንት ከሰዓት በኋላ 9 ሰዓት ላይ በዋለው ችሎት ተከሳሹ ፖሊስ በተከሰሰበት ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ…

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር  ሊግ ዛሬ በተደረገ ጨዋታ ወላይታ ዲቻ ድል ቀንቶታል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ28ኛው ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ወላይታ ዲቻ ጅማ አባ ጅፋርን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ ረፋድ ላይ በተደረገው ጨዋታ ጅማ አባ ጅፋር በመሱድ መሀመድ ጎል እስከ እረፍት መምራት ቢችሉም ከረፍት መልስ አበባየሁ አጂሶ…

ኔቶ ዓለምን በተፅዕኖው ስር ለመክተት የሚያደርገውን መሰፋፋት በንቃት መከታተል እንደሚገባ የኢራኑ ፕሬዚዳንት አስገነዘቡ

አዲስ አበባ፣ሰኔ 16፣2014 (ኤፍ ቢሲ) የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት/ኔቶ/ ዓለምን በተፅዕኖው ስር ለመክተት የሚያደርገውን መስፋፋት በንቃት መከታተል እንደሚገባ የኢራኑ ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ አስገነዘቡ። ፕሬዚዳንቱ ከሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስርጌ ላቭሮቭ ጋር በወቅታዊ…

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ባህርዳር ከተማ ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በ28ኛ ሳምንት በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ባህርዳር ከተማ ድሬዳዋ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡ በሜዳው እና በደጋፊው ፊት ጨዋታውን ላደረገው ባህርዳር ከተማ መናፍ አወል ብቸኛዋ የማሸነፊያ ጎል ማስቆጠር ችሏል፡፡ የጣና ሞገዶቹ ዘሬ…

ሳዑዲ አረቢያ በኮቪድ 19 ምክንያት በአራት ሀገራት ላይ ጥላው የነበረውን የጉዞ እገዳ አነሳች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሳዑዲ አረቢያ በኮቪድ 19 ምክንያት በቱርክ፣ ህንድ፣ ኢትዮጵያ እና ቬትናም ላይ ጥላው የነበረውን የጉዞ እገዳ ማንሳቷን አስታውቃለች፡፡ የሀገሪቱ የዜና ተቋም ኤስ ፒ ኤ እንደዘገበው በወሩ መጀመሪያ ላይ ሳዑዲ አረቢያ በቤት ውስጥ የፊት ጭምብል…

ፋሲል ከነማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ በካፍ የክለቦች ውድድር ኢትዮጵያን ይወክላሉ

አዲስ አበባ፣ሰኔ 13፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በተደረገ ጨዋታ ፋሲል ከነማ አዳማ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡ ረፋድ በተደረገው ጨዋታ የፋሲልን የማሸነፊያ ጎሎች ሙጂብ ቃሲም ከዕረፍት መልስ አስቆጥሯል፡፡ አጼዎቹ ዛሬ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ነጥባቸውን 55…

በፕሪሚየር ሊጉ ጅማ አባ ጅፋር እና ፋሲል ከነማ ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ26ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጅማ አባ ጅፋር ሃድያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡ ረፋድ ላይ በተደረገው ጨዋታ አንጋፋው ዳዊት እስጢፋኖስ ከረጅም ጊዜ በኋላ ባስቆጠራት ጎል ጅማ አባ ጅፋር ሙሉ ሶስት ነጥብ ማግኘት ችሏል፡፡…

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ምርታማነትን የሚያረጋግጡ 37 ትራክተሮችን ለክልሎች አከፋፈለ 

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ 37 ትራክተሮችን ለተለያዩ ክልሎች አከፋፍሏል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለሶማሌ፣ ኦሮሚያ፣ አማራ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ነው ድጋፉን ያደረገው። ድጋፋ በዋናነት…

የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ሀይል በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እንዲሰማራ ፕሬዚዳንት ኬንያታ ጠየቁ 

አዲስ አበባ፣ሰኔ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ሀይል በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እንዲሰማራ የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጠይቀዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍል ያለበትን የፀጥታ ችግር ወደ ነበረበት ለመመለስ በማሰብ ነው የቀጠናው ተጠባባቂ…

ሩሲያ በሴቬሮዶኔስክ ከተማ የመሸጉ የዩክሬን ወታደሮች እጅ እንዲሰጡ ጠየቀች 

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ በሴቬሮዶኔስክ ከተማ በተለይም በኬሚካል ፋብሪካ ውስጥ የመሸጉ የዩክሬን ወታደሮች ትጥቃቸውን እንዲያወርዱና እጅ እንዲሰጡ ጠየቀች፡፡ የከፋ ደም- አፋሳሽ በተባለው የሴቬሮዶኔስክ  ውጊያ የሩሲያ ወታደራዊ ኃይሎች አብዛኛው የዩክሬን ጦር ከምሥራቃዊቷ…